በአዲስ አበባ  ሲካሄድ የቆየው የምስራቅ አፍሪካ ጳጳሳት የሲኖሳዊ ትግበራ የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ። በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የምስራቅ አፍሪካ ጳጳሳት የሲኖሳዊ ትግበራ የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ። 

በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የምስራቅ አፍሪካ ጳጳሳት የሲኖሳዊ ትግበራ የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ።

በኢትዮጵያ ብፁዓን ጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽህፈት ቤት እና በምስራቅ አፍሪካ የብፁዓን ጳጳሳት ጉባኤ ህብረት ‘አመስያ’ አስተባባሪነት አዲስ አበባ በሚገኘው የኮንሶላታ ማርያም አባቶች ገዳም ከመስከረም 19 እስከ 22 2018 ዓ.ም. ድረስ በተካሄደው የምክክር ጉባኤ ላይ የህብረቱ አባል ሃገራት ብፁዓን ጳጳሳት ተገኝተዋል።

አቅራቢ ዘላለም ኃይሉ ፥ አዲስ አበባ

መቀመጫውን ናይሮቢ ኬንያ ያደረገው የምስራቅ አፍሪካ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት ጉባኤ ህብረት አሜስያ (AMECEA) እንደሚታወቀው በምስራቅ አፍሪካ ያሉ ዘጠኝ ሀገራትን ማለትም ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ማላዊ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳ እና ዛምቢያ ውስጥ ያሉ ብሔራዊ የጳጳሳት ጉባኤዎች ህብረት የሆነ የካቶሊክ አገልግሎት ድርጅት ነው።  

የምስራቅ አፍሪካ የብፁዓን ጳጳሳት ጉባኤ ህብረት አባል ሃገራት የተሳተፉበት እና በጳጳሳት ደረጃ በተካሄደው በዚህ የምክክር ጉባኤ በሲኖዶሳዊነት ሂደት ወቅት የነበራቸውን የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበት እና ቀጠናዊ አቅጣጫ የሚያስቀምጡበት ሲሆን፥ በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሊቀ ጳጳሳት ዘካቶሊካዊያን እና የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጳጳሳት ጉባኤ ፕረዚዳንት እንዲሁም የጠቅላይ ጽህፈት ቤት ጠቅላይ ጸኃፊን ጨምሮ በጉባኤው ላይ የህብረቱ አባል ሀገራት የሆኑት የዘጠኙ ሃገራት የጳጳሳት ተወካዮች ተሳትፈዋል።

የምስራቅ አፍሪካ የጳጳሳት ጉባኤ የሲኖዶሳዊነት ትግበራን በተመለከተ በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የምክክር ጉባኤ የምስራቅ አፍሪካ የጳጳሳት ጉባኤ ህብረት የሆነው አመስያ (AMECEA) ላለፉት አራት ዓመታት በዝግጅት ላይ ቆይቶ እ.አ.አ. በ 2024 ዓ.ም. ጥቅምት ወር ላይ የተጠናቀቀውን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ የትግበራ ሰነድ ሂደትን አስመልክቶ የምክክር ጉባኤ ማድረጉ ተነግሯል።

በኢትዮጵያ ጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽህፈት ቤት እና በአሜስያ አስተባባሪነት በአዲስ አበባ የኮንሶላታ ማርያም አባቶች ገዳም ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ የሲኖዶሳዊነት ሰነድን በተግባር ላይ ለማዋል ከቅድስት መንበር በወጣው አቅጣጫ ላይ መሰረት በማድረግ ብፁዓን ጳጳሳቱ ውይይት አድርገዋል።

በጳጳሳት ደረጃ የተካሄደው ይህ የምክክር ጉባኤ በሲኖዶሳዊነት ሂደት ወቅት ሀገራቱ የነበራቸውን ልምድ ልውውጥ ያደረጉበት፣ በሂደቱም የገጠማቸውን ተግዳሮት የተወያዩበት እና ቀጠናዊ አቅጣጫ የሚያስቀምጡበት መሆኑም ተገልጿል።

የአሜስያ ጽህፈት ቤት የማህበራዊ ተግባቦት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ክቡር አባ አንድሪው ካውፋ የስብሰባው ዋና ዓላማ የሲኖዶሳዊነት ትግበራ ሂደትን መገምገም መሆኑን ገልጸው፥ ቅድስት መንበር ባስቀመጠችው መርሃ-ግብር መሰረት እ.አ.አ እስከ 2027 ዓ.ም. ድረስ ሁሉም የጳጳሳት ጉባኤዎች የሲኖዶስ ሰነድን በተግባር ላይ ማዋል እንዳለባቸው አጽንዖት ሰጥተው የገለጹ ሲሆን፥ አክለውም እንደተናገሩት እ.አ.አ. በ2028 ዓ.ም. በቫቲካን ለሚካሄደው ጉባኤ በሀገራት፣ በቀጠናቸው እና በአህጉር ደረጃ የተሰሩ ሥራዎች እንደሚቀርቡም ጭምር ገልጸዋል።

ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን በበኩላቸው የሲኖዶሳዊነት ሰነድ በተግባር ላይ ለማዋል ሁሉም የቤተክርስቲያን አካላት በቅድሚያ ሰነዱን በጥልቀት ማንበብ እንደሚገባቸው አሳስበው፥ ይህንንም በማድረግ የቤተክርስቲያን መሰረት በሆነው እውነተኛ ቤተሰብ ላይ መስራት እንደሚያስፈልግ የገለጹ ሲሆን፥ በቀጠናው ከፍተኛ ቁጥር የያዘውን ወጣቶችን በሲኖዶሳዊ አብሮነት መንፈስ መጠበቅ እና መንክባከብ እንደሚያስፈልግ እና የሲኖዶሳውነት ሰነድ በተግባር ላይ ለማዋል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከቤተክርስቲያን ጋር እንዲተባበር ጥሪ አቅርበዋል።

ለሶስት ተከታታይ ቀናት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የሲኖዶሳዊነት የትግበራ ሂደትን በተመለከተ በአዲስ አበባ የኮንሶላታ ማርያም አባቶች ገዳም ሲካሄድ የቆየው የምክክር መድረክ የተለያዩ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተጠናቀቀ ሲሆን፥

የሲኖዶሳዊነት ሰነድን በተግባር ላይ ለማዋል እና የቤተክርስቲያን መመሪያ በቀጣይ ተፈጻሚ እንዲሆን አስቻይ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ይህን ሰነድ ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እና ተግባራዊነቱን ለማረጋገጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሲሆን፥ የአሜስያ ጽህፈት ቤት በበኩሉ በሲኖድ ሰነድ አቅጣጫ መሰረት በቀጣይ የሚኖሩ በርካታ የውይይት፣ የግምገማ እና የአፈጻጸም ክትትል መድረችኮን እንደሚያዘጋጅ ገልጿል።

ጉባኤውን የመሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ረዳት ጳጳስ ይህ ጉባኤ የሲኖዶሳዊነት አተገባበር በቀጠናው የተቀናጀ ለማድረግ የተካሄደ መሆኑን የጠቆሙ ሲሆን፥ በስብሰባው የተሳተፉት ብፁዓን ጳጳሳት ከዚህ ቀደም አሜስያን እና ሀገራቸውን በመወከል በቅድስት መንበር የተገኙ ተወካይ ጳጳሳትን መሆናቸውን ገልጸዋል። በስብሰባው ማጠቃለያም የቅድስት መንበርን መመሪያ መሰረት በማድረግ የአሜስያ የሲኖዳስዊነት ትግበራ አጋዥ ሰነድ እንደሚወጣም ያሳወቁ ሲሆን፥ ጉባኤው አዲስ አበባ እንዲሆን የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበል ለጋበዙት ለብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ፣ የአሜስያ ጽህፈት ቤት እንዲሁም በአዲስ አበባ ለነበራቸው መልካም ቆይታ ለጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽህፈት ቤት እና ለኮንሶላታ አባቶች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በጉባኤው በማጠቃለያ መርሃግብር በኢትዮጵያ የቅድስት መንበር ተወካይ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ብሪያን ኡዳግዌ ተገኝተው አባታዊ ቡራኬ የሰጡ ሲሆን፥ በመጨረሻም የጉባኤው ተሳታፊ ብፁዓን ጳጳሳት የአድዋ ሙዚየምን እና የኢዮቤልዩ ቤተመንግስት ጉብኝት በማድረግ ተጠናቋል ።

 

 

Photogallery

በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የምስራቅ አፍሪካ ጳጳሳት የሲኖሳዊ ትግበራ የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ።
03 Oct 2025, 13:48