ር.ሊ.ጳ ሊዮ AI በሐኪሞች እና በበሽተች መካከል ያለውን ግንኙነት በፍጹም ሊተካ አይችልም አሉ!
የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ ሐሙስ ዕለት መስከረም 22/2018 ዓ.ም ለላቲን ኢቤሮ-አሜሪካን እና ለካሪቢያን የሕክምና ኮንፌዴሬሽን (CONFEMEL) አባላትን በቫቲካን አቀባበል አድርገውላቸዋል፣ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለመስጠት ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል እና የአገልግሎቶቻቸውን ጥሪ ጥልቅ ሰብዓዊ ገጽታ እንዲጠብቁ አክለው አበረታችኋል።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ከላቲን አሜሪካ፣ ከአይቤሪያ ባሕረ ገብ መሬት እና ከካሪቢያን አገሮች የተውጣጡ ሐኪሞችን አሰባስቦ የያዘውን የላቲን ኢቤሮ-አሜሪካን እና የካሪቢያን የሕክምና ኮንፌዴሬሽን በእንግሊዘኛው ምጻረ ቃል (CONFEMEL) ተወካዮችን ሰላምታ አቅርበዋል። "ለዚህ ደከመኝ ሰለቸኝ በማለት ሳትታክቱ ለምታከናውኑት ሥራ እናመሰግናለን" በማለት ቅዱስነታቸው አክለው ተናግረዋል።
በእለቱ በመስከረም 02/2018 ዓ.ም ቤተክርስቲያን የቅዱሳን ጠባቂ መላዕክትን መታሰቢያ እንደምታከብር በማስታወስ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በስፍራው የተገኙት ስለ ሀኪም እና ታካሚ ግንኙነት እንዲያሰላስሉ ጋብዘዋቸዋል፣ ይህም በግላዊ ግንኙነት እና በጤና አጠባበቅ ላይ የተመሰረተ ነው ያሉ ሲሆን ቅዱስ አውግስጢኖስን በመጥቀስ "ክርስቶስን እንደ ሐኪም እና መድኃኒት ጠቅሶታል፡- በላቲን ቋንቋ “Ipse medicus፣ ipse medicamentum” (ሐኪሙ ራሱ፣ መድሃኒቱም ራሱ)" በማለት ኢየሱስ “ቃል ነውና ባለ መድኃኒት ነው፤ ቃልም ሥጋ ስለ ሆነ መድኃኒት” እንደሆነ ገልጿል።
አክለውም "በሽታዎችን ለማከም ከሚጠቀሙት መሳሪያዎችና ዕቃዎች ባሻገር በሕክምና ግንኙነት ውስጥ ውይይት፣ ኮሙኒኬሽን እና አካላዊ ንክኪ ሁል ጊዜ መገኘት አለባቸው" ብለዋል።
የፈውስ ንክኪ
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ኢየሱስ የሥጋ ደዌ በሽተኞችን በፈወሰበት የወንጌል ክፍል ላይ በማሰላሰል (ማርቆስ 1: 40–42) ይህ “አካላዊ መገለጫ ምልክት ብቻ አይደለም” ነገር ግን “በለምጻሙና በኢየሱስ መካከል ግላዊ ዝምድና የተፈጠረበት ነው፤ ሰዎች ሊነኩት የማይፈልጉት ሰው ከኢየሱስ እንክብካቤ ጤናና መዳን የሚያገኝ” መሆኑን ጠቁመዋል።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በተጨማሪም “በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በቬንዙዌላ ውስጥ ከታወቁት ሐኪሞች መካከል አንዱ የሆነውን ብፁዕ ሆሴ ግሪጎሪዮ ሄርናንዴዝ የሕክምና ብቃታቸውን እና እጅግ በጣም ለተቸገሩ ሰዎች ራሳቸውን ከመሰጠት ጋር በማጣመር “የድሆች ሐኪም” የሚል ማዕረግ እንዳገኙ በመግለጽ የሰጡትን ምሳሌ አስታውሰዋል።
ቴክኖሎጂ እና የሰው ቅርበት
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በመቀጠል ወደ ሰው ሰራሽ የማሰብ ችሎታ በሕክምና ውስጥ ያለውን ሚና ሐሳባቸውን በማዞር ክሊኒካዊ እንክብካቤን ለማሻሻል ትልቅ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል። ሆኖም “የሐኪሙን ቦታ በፍፁም ሊወስድ እንደማይችል ገልጸው፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ 16ኛን በመጥቀስ፣ ‘የፍቅር የውኃ ማጠራቀሚያዎች፣ ለሚሰቃዩ ሰዎች መረጋጋትና ተስፋን የሚሰጥ’ በማለት ገልጸዋቸዋል። ስልተ ቀመር የመቀራረብ ምልክትን ወይም የመጽናኛ ቃልን ፈጽሞ ሊተካ አይችልም" ብሏል።
ወደፊት ያለውን መንገድ ተስፋ አድርግ
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉ የሕክምና ባለሙያዎች የሚያጋጥሟቸውን “ታላቅና አነቃቂ ተግዳሮቶች” አምነው በተስፋ እንዲጋፈጡ አበረታቷቸዋል። “ተስፋችን” የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን እና የታመሙትን ለቅድስት ድንግል ማርያም በአደራ በመስጠት “በዚህ ምድራዊ ጉዞ ሁላችንም ወደ አብ ቤት መጓዝ እንችል ዘንድ" እርሷ በአማላጅነቷ ትርዳን" ካሉ በኋላ ቅዱስነታቸው መልእክታቸውን አጠናቀዋል።
