ር.ሊ.ጳ ሊዮ ስልጣን እና ኃይል ደስታን አያጎናጽፉም፣ ለልባችን መሻት መልስ የሚሰጠው ክርስቶስ ብቻ

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ “ኢየሱስ ክርስቶስ ተስፋችን ነው!” በሚለው የኢዮቤልዩ ዓመት መርህ ሐሳብ ላይ በመመርኮዝ ሳምንታዊ የጠቅላላ ትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ በየሣምንቱ በተከታታይ እያደረጉ እንደሚገኝ ከዚህ ቀደም መግለጻችን ይታወሳል። በዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተገኙ ምዕመናን ረቡዕ ጥቅምት 05/2018 ዓ.ም ያደረጉት የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ "የክርስቶስ ትንሳኤ እና የዛሬው አለም ተግዳሮቶች" በተሰኘው ዐብይ አርስት ሥር "ከሙታን የተነሣው ጌታ የሰው ልጅ ተስፋ ሕያው ምንጭ" በተሰኘ ንዑስ አርስት የቀረበ የክፍል አንድ አስተምህሮ እንደ ነበረ የተገለጸ ሲሆን ስልጣን እና ኃይል ደስታን አያጎናጽፉም፣ ለልባችን መሻት መልስ የሚሰጠው ክርስቶስ ብቻ ነው ማለታቸው ተገልጿል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

በዕለቱ የተነበበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል

ኢየሱስ መልካም እረኛ እንደሆነ

ኢየሱስም ደግሞ አላቸው “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ እኔ የበጎች በር ነኝ። በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፤ ይገባልም፤ ይወጣልም፤ መሰማሪያም ያገኛል። ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድና ሊያጠፋ እንጂ ለሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወትን እንዲያገኙ፥ የተትረፈረፈ ሕይወትን እንዲያገኙ መጣሁ" (ዩሐንስ 10፡7.9-10)።

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በወቅቱ ያደረጉትን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

የኢዮቤልዩ ዓመትን ምክንያት በማድረግ እስካሁን እያደረግን ባለነው የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ  ቅዱሳት ወንጌላትን ተከትለን፣ የኢየሱስን ሕይወት፣ ከልደቱ እስከ ሞቱና ትንሣኤው ድረስ በጥልቀት ተመልክተናል። ይህንንም በማድረግ የተስፋ ጉዟችን ጠንካራ መሰረት እና አስተማማኝ መንገድ አግኝቷል። እንግዲህ በጉዞው የመጨረሻ ክፍል፣ በትንሳኤው የሚደመደመው የክርስቶስ ምሥጢር፣ የድኅነት ብርሃኑን ከዘመኑ ሰብዓዊና ታሪካዊ እውነታዎች ጋር በማገናኘት፣ ከጥያቄዎቹና ተግዳሮቶቹ ጋር እንዲያበራ እንፍቀድለት።

ይህንን ዝግጅት በድምጽ ለማዳመጥ ተጫወት የሚለውን ምልክት ይጫኑ

ሕይወታችን በተለያዩ ልዩነቶች እና ልምዶች የተሞላ ስፍር ቁጥር በሌላቸው ክስተቶች የታጀበ ነው። አንዳንድ ጊዜ ደስተኛ፣ ሌላ ጊዜ ሐዘንተኛ፣ ሌላ ጊዜ ኑሮ እንደተሟላልን እናስባለን፣  ወይም ጭንቀት፣ እርካታ ወይም ዝቅ ያለ ስሜት ይሰማናል። በተጨናነቀ ሕይወት እንኖራለን፣ ውጤት ለማምጣት በምያስችሉ ጉዳዮች ላይ እናተኩራለን፣ እንዲያውም ከፍ ያሉ፣ የተከበሩ ግቦች ላይ ለመድረስ እንጣጣራለን። በአንጻሩ፣ የታገድን፣ ተቆርቋሪ፣ የዘገየ ወይም ጨርሶ ያልተሳካ ስኬትን እና እውቅናን እየጠበቅን እንቆያለን። በአጭር አነጋገር፣ እኛ ራሳችንን ተጻራሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እናገኛለን፣ ደስተኛ ለመሆን እንፈልጋለን፣ ነገር ግን ያለ ምንም ጥላ ከለላ ቀጣይነት ባለው መንገድ ደስተኛ ለመሆን በጣም ከባድ ነው። ውስን ከመሆነው ማንነታችን ጋር ተስማምተናል እና በተመሳሳይ ጊዜ፣ ውስንነታችንን ለማሸነፍ ስንሞክር ሊተገበር በማይቻል ፍላጎት ውስጥ እንገባለን። ሁል ጊዜ የሆነ ነገር እንደሚጎድለን ጥልቅ ስሜት ይሰማናል።

በእውነት ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ በተናገረው አገላለጽ (ዩሐ. 10፡10) እንደሚለው፣ በሙላት፣ በኑሮ እንድንደሰት እና የተትረፈረፈ ሕይወት አግኝተን እንድንደሰት እንጂ በጎደለን ነገር እንድናዝን አልተፈጠርንም።

በልባችን ውስጥ ያለው ይህ ጥልቅ ፍላጎት የመጨረሻውን መልስ ሊያገኝ በሚችለው ሚና ላይ ሳይሆን በስልጣን ወይም በማግኘት ሳይሆን ለዚህ የሰው ልጅ መነሳሳት የሚያረጋግጥ ሰው እንዳለ በእርግጠኝነት በማወቅ ነው። ይህ መጠበቅ ተስፋ እንደማይቆርጥ ወይም እንደማይደናቀፍ በመገንዘብ። ይህ እርግጠኝነት ከተስፋ ጋር ይጣጣማል። ይህ ማለት ባለብሩህ ተስፋነትን ማሰብ ማለት አይደለም፡ ብዙ ጊዜ ብሩህ ተስፋ፣ ተስፋ እንድንቆርጥ ያደርገናል፣ ይህም የምንጠብቀው ነገር እንዳይሟላ ያደርጋል፣ ነገር ግን ተስፋ ቃል ገብቷል እና ይፈጸማል።

እህቶቼ እና ወንድሞቼ፣ ከሙታን የተነሳው ኢየሱስ የዚህ መዳን ዋስትና ነው! እርሱ ጥማችንን የሚያረካ ምንጭ፣ መንፈስ ቅዱስ በልባችን ውስጥ የሚያስገባው ወሰን የለሽ የሙላት ጥማት ነው። በእርግጥ የክርስቶስ ትንሳኤ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ቀላል ክስተት ሳይሆን ከውስጥ የመለወጥ ክስተት ነው።

ስለ የውሃ ምንጭ እናስብ። ባህሪያቱ ምንድን ናቸው? ጥምን ያረካል፣ ፍጥረታትን ያድሳል፣ መሬቱን ያረሰርሳል፣ ፣ ለም ያደርገዋል እንዲሁም መካን የሆነውን ፍሬያማ ሆኖ እንዲኖር ያደርጋል።  ለደከመው መንገደኛ እረፍት ይሰጠዋል፣ የደስታን ውቅያኖስ ደስታ ያሰኛል። የጉድጓድ ምንጭ ለተፈጥሮ፣ ለፍጡራን፣ ለሰው ልጆች በነጻ የሚሰጥ ስጦታ ሆኖ ይታያል። ውሃ ከሌለ መኖር አይቻልም።

ከሙታን የተነሣው ጌታ የማይደርቅ፣ የማይለወጥ ሕያው ምንጭ ነው። ሁል ጊዜ ንጹህ እና ለተጠማ ማንኛውም ሰው ዝግጁ ሆኖ ይቆያል። የእግዚአብሔርን ምሥጢር ባጣን መጠን ሙሉ በሙሉ ሳንጠግብ ወደ እርሱ ይበልጥ እንማርካለን። ቅዱስ አውግስጢኖስ በአሥረኛው የኑዛዜ መጽሐፍ ላይ ይህን የማይነጥፍ የልባችንን ናፍቆት በትክክል በመያዝ በታዋቂው የውበት ዝማሬው እንዲህ ሲል ገልጾታል፡- “ጠረን ያለው ነገር ተነፈስክ፣  እኔም ያንን ጠረን ሳብኩኝ፣ ከአንተ በመቀጠል መልሼ ተነፈስኩኝ፣ ቀመስኩትና ተራብኩኝ፣ ተጠማው። ዳሰስከኝና ሰላምህን ለማግኘት ተቃጠልኩኝ" ሲል ጽፏል።

ኢየሱስ፣ ከትንሣኤው ጋር፣ የሕይወትን ቋሚ ምንጭ አረጋግጦልናል፣ እርሱ ሕያው ነው (ራዕ. 1፡18)፣ ሕይወትን የሚወድ፣ ሞትን ሁሉ የምያሸንፍ ነው። ስለዚህ፣ በምድራዊ ጉዟችን እረፍት ሊሰጠን እና ለዘላለም ፍጹም ሰላም እንደሚኖረን ያረጋግጥልናል። ለልባችን ጥልቅ ጥያቄዎች መልስ የመለሰው የሞተውና የተነሣው ኢየሱስ ብቻ ነው፤ በእርግጥ መድረሻ አለን ወይ? የእኛ መኖር ትርጉም አለው ወይ? የብዙ ንጹሐንን ስቃይ እንዴት ይቤዣል?

ከሙታን የተነሳው ኢየሱስ “ከላይ” መልስ አልሰጠንም፣ ነገር ግን በዚህ ብዙ ጊዜ አስቸጋሪ፣ አሳማሚ እና ምስጢራዊ በሆነ ጉዞ አጋራችን ይሆናል። ጥማችንን መቋቋም ሲያቅተን ባዶ የውሃ መያዣችንን ሊሞላ የሚችለው እሱ ብቻ ነው።

የጉዟችንም መዳረሻ እርሱ ነው። ያለ ፍቅሩ የሚደረግ የህይወት ጉዞው፣ ያለ ግብ የሚንከራተት፣ መዳረሻ ያጣ አሳዛኝ ስህተት ይሆናል። እኛ ደካማ ፍጥረታት ነን። ስህተቶች የሰውነታችን አካል ናቸው፣ እንድንወድቅ፣ እንድንተው፣ ተስፋ እንድንቆርጥ የሚያደርገው የኃጢአት ቁስል ነው። ይልቁንስ መነሳት ማለት ተነስተን በእግራችን መቆም ማለት ነው። ከሙታን የተነሣው የመዳረሻችንን ዋስትና ይሰጠናል፣ ወደ ቤቱ ይመራናል፣ የምንጠበቅበት፣ የምንወደድበት እና የምንድንበት መንገድ እርሱ ነው። ከእርሱ ጋር መጓዝ ማለት ሁሉም ነገር እንዳለ ሆኖ መቆየቱን መለማመድ፣ ጥማችንን ማጥፋት እና እንደ ከባድ ድንጋይ ታሪካችንን ሊያደናቅፍ ወይም ሊያዘናጋን በሚችል መከራና ተጋድሎ መታደስ ማለት ነው።

ውድ ጓደኞቼ፣ ከክርስቶስ ትንሳኤ የህይወት ድካም ቢያጋጥመንም፣ ጥልቅ እና አስደሳች መረጋጋት፣ ከእርሱ ብቻ ፍጻሜ የሌለው ሰላም የሚሰጠን የቅድመ-ቅምሻ ተስፋ ያመነጫል።

 

Photogallery

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ
15 Oct 2025, 15:18

በቅርብ ጊዜ ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የተደረገው ግንኙነት

ሁሉንም ያንብቡ >