ዝነኞቹ የሆሊውድ ተዋናዮች  ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ጋር በቫቲካን መገናኘታቸው ተገለጸ! ዝነኞቹ የሆሊውድ ተዋናዮች ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ጋር በቫቲካን መገናኘታቸው ተገለጸ!  (@Vatican Media)

ዝነኞቹ የሆሊውድ ተዋናዮች ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ጋር በቫቲካን መገናኘታቸው ተገለጸ!

ዝነኞቹ የሆሊውድ ተዋናዮች ኬት ብላንቼት፣ ስፓይክ ሊ፣ ሌስሊ ማን እና ኬኔት ሎነርጋን ቅዳሜ ዕለት ሕዳር 6/2018 ዓ.ም በቫቲካን ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ጋር መገናኘታቸው የተገለጸ ሲሆን ከግንኙነታቸው በኋላ ከቫቲካን የዜና አገልግሎት ጋር በነበራቸው ቆይታ በሲኒማ ዓለም ውስጥ ያላቸውን ሚና ሌሎችን ለመርዳት እንዲጠቀሙበት ላቀረቡላቸው ጥሪ የሰጡትን ምላሽ ያካፈሉ ሲሆን “ለሰው ልጅ ሙሉ በሙሉ ለመኖር አስፈላጊ የሆነውን የተስፋ ክፍል እንደገና እንዲያገኙ” ሲኒማ አጋዥ መሣርያ እንደሆነ ገልጸዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

“ታሪኩ ይኸውልህ… ብዙውን ጊዜ ተራኪዎች ስራቸውን ሲያብራሩ የሚሰሙት ነገር ነው። እና በፈጠራ ሥራ አርቲስቶች እና በሲኒማ ባለሙያዎች በተሞላ ክፍል ውስጥ፣ ሁልጊዜ የሚነገር ታሪክ አለ። የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት  ሊዮ 14ኛ ስለ ፊልሞች ውበት፣ አስፈላጊነት እና በሲኒማ ዓለም ውስጥ የተሳተፉ ሰዎች ኃላፊነት ንግግር ካዳመጡ በኋላ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የታወቁ ተዋናዮች እና የፊልም ማለሙያዎች በቫቲካን የሐዋርያዊ ቤተ መንግሥት አዳራሽ ሞልተው የራሳቸውን እና የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትን ገጠመኝ ታሪኮችን እያነሱ እያንዳንዳቸው ይተርካሉ።

ከአሜሪካዊቷ ተዋናይት ሌስሊ ማን ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

በማህበረሰቡ ልብ ውስጥ

በተከታታይ የድርጊት መተግበሪያዎች (streaming apps) ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ፣ በዓለም ዙሪያ የሲኒማ ታዳሚዎች ቁጥር እ.አ.አ በ2024 ዓ.ም በ8.8% ቀንሷል - ይህም እ.አ.አ ከ2023 ዓ.ም በ500 ሚሊዮን ያነሰ ሽያጭ አስመዝግቧል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ "ሲኒማ ቤቶች እና ቲያትሮች የማህበረሰባችን ልብ ናቸው" በማለት የዚህ ውድቀት አደጋን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴታቸውን እና እነሱን የመጠበቅን አስፈላጊነት አረጋግጠዋል።

አሜሪካዊቷ ተዋናይት ሌስሊ ማን ይህንን ፈተና በቁም ነገር ወስዳዋለች። እንደ ተዋናይት፣ ሰዎች በሲኒማ ቤቶች እና በቲያትር ቤቶች እንዲመለከቱ፣ "በቤት ውስጥ ከመሆን ይልቅ አብረው ፊልሞችን ማየት እንዲለማመዱ" ለማድረግ እየሞከረች እንደሆነ ተናግራለች።

ተዋናይት ሌስሊ ማን የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን የወደፊት መጻይ ጊዜ በተስፋ ስሜት ለመመልከት ያቀረቡትን ጥሪ ለመከተል እየመረጡ ነው፡- "ለሲኒማ የወደፊት ጊዜ በጣም ተስፋ እናደርጋለን እና በጣም ጓጉተናል" ሲሉ ቅዱስነታቸው መናገራቸውን አብራርተዋል። የጳጳሱ ቃላት በጣሊያንኛ ቢሆኑም፣ ተዋናይት ሌስሊ ማን ከቫቲካን የዜና አገግልግሎት በነበራት ቆይታ ምን ያህል በሚያስደንቅ ሁኔታ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩ አጋርተዋል። "በጣም አስደናቂ ነበር" ሲሉ ወደ ቤት ሄደው የእንግሊዝኛውን ትርጉም እንደሚያነቡ ገልጸዋል።

ቤተክርስቲያን እና ሲኒማ

ይህ የተስፋ ስሜት በአሜሪካዊው ጸሐፊ፣ የፊልም ደራሲ እና የፊልም ዳይሬክተር ኬኔዝ ሎነርጋን በበኩላቸው ሲናገሩ ምንም እንኳን ክርስቲያን፣ ካቶሊክ ወይም ሃይማኖተኛ ባይሆኑም፣ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን “ለብዙ መቶ ዓመታት የኪነጥበብ ታላላቅ አራማጆች አንዷ” መሆኗን ጠቁመዋል።

አሜሪካዊው ጸሐፊ፣ የፊልም ደራሲ እና የፊልም ዳይሬክተር ኬኔዝ ሎነርጋን ሲኒማ ወደዚያ የኪነጥበብ ባህል ለማምጣት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ያላቸውን ፍላጎት አድንቀዋል። ጥበብ፣ ፊልም፣ ሥዕል፣ ሙዚቃ የሌለበት ዓለም “በጣም የሚያሳዝን ዓለም ይሆናል” ሲሉ ቅዱስነታቸው መናገራቸውን ገልጿል። በዛሬው የግጭቶች እና የማህበራዊ ውጥረቶች በተሞላው ዓለም፣ ኪነጥበብ - በተለይም ሲኒማ - የተስፋ መንገድ ሊሆን ይችላል። “ሰዎች ተስፋ የመፍጠር እድል እንዳገኙ” አሜሪካዊው ጸሐፊ፣ የፊልም ደራሲ እና የፊልም ዳይሬክተር ኬኔዝ ሎነርጋን ተናግሯል።

ፊልሞችን በመስራት እና ከትዕይንቱ በስተጀርባ መሳተፍ “ትልቅ መብት ነው” ሲሉ የተናገሩት አሜሪካዊው ጸሐፊ፣ የፊልም ደራሲ እና የፊልም ዳይሬክተር ኬኔዝ ሎነርጋን ይህም መዝናኛ እና ትርጉም ለሚፈልጉ ሰዎች የውበት፣ የእውነት እና የተስፋ ምስክርነት ሊሆን ይችላል ብለዋል።

ከቤት ብዙም አይርቅም

በሊቀ ጳጳሱ ንግግር መጨረሻ ላይ የተለያዩ አርቲስቶች በተናጥል ከቅዱስነታቸው ጋር መገናኘታቸው የተገለጸ ሲሆን የተለያዩ ስጦታዎችን ለቅዱስነታቸው ማቅረባቸውም ተገልጿል።

ከአሜሪካዊው የፊልም ሰሪ ስፓይክ ሊ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

ሲኒማ ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ ይሆናል

የአውስትራሊያ ተዋናይ እና የፊልም አምራች ኬት ብላንቼት እድሉን ተጠቅማ ለርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ውብ ትርጉም ያለው ትንሽ ሰማያዊ አምባር በስጦታ መልክ ማቀረቧ የተገለጸ ሲሆን “እኔ ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኤጀንሲ፣ ከ"UNHCR" ጋር እሰራለሁ” በማለት የተናገሩት አርቲስት ብላንቼት፣ እናም አምባሩ “ከተፈናቀሉ ሰዎች ጋር በመተባበር የምታደርገው” አንባር መሆኑ አስረድተዋል።

በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ አርቲስት ብላንቼት የUNHCR በጎ ፈቃድ አምባሳደር በመሆን የተፈናቃዮችን የፊልም ፈንድ አስጀምሯል። ይህ ተነሳሽነት “የተፈናቀሉ የፊልም ሰሪዎችን ስራ ወይም የተፈናቀሉ ሰዎችን ተሞክሮ በመጻፍ ረገድ የተረጋገጠ ታሪክ ያላቸውን የፊልም ሰሪዎችን” ለመደገፍ እና ለማበረታት ቁርጠኛ የሆነ ነው።

አርቲስት ብላንቼት ከዓለም አቀፉ የፊልም ፌስቲቫል ሮተርዳም ዳይሬክተር ቫንጃ ካልድጄርሲች ጋር በመሆን የእነዚህ የስደተኛ ፊልም ሰሪዎች ድምጽ “ብዙውን ጊዜ ከዋና ዋናዎቹ ይገለላል” ብለዋል። ስለዚህ አርቲስት ብላንቼት እና ካላድጄርሲች የፈንዱን ስራ ከቅዱስ አባታችን ጋር መጋራት አስፈላጊ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።

“ቅዱስነታቸው ይህንን የውይይት ቦታ መክፈታቸው እና ብዙ ጊዜ የማይሰሙትን እና እንደ ተፈናቃዮቹ ፊልም ሰሪዎች ብዙ እድል የሌላቸውን ሰዎች ታሪክ ለመፍጠር ቦታ መፍጠር ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ መጠቆም እጅግ አስፈላጊ ነው” ሲሉ ካላድጄርሲክ አፅንዖት ሰጥተው የተናገሩ ሲሆን ይህ ደግሞ መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን እና የእያንዳንዱን ሰው ክብር ስለሚያበረታቱ በተፈናቃዮች ፊልም ፈንድ እና በቫቲካን መካከል ያለውን የጋራ እሴቶች ያሳያል ሲሉ አክለው ተናግረዋል።

የግዳጅ መፈናቀል ዛሬ ዓለማችን እያጋጠማት ያለ አስፈላጊ የሰብአዊነት ጉዳይ ነው። በእንግሊዜኛው ምጻረ ቃል "UNHCR" (የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን) እ.አ.አ በሰኔ 2025 መጨረሻ ላይ በዓለም ዙሪያ ወደ 117 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በስደት፣ በግጭት፣ በዓመፅ፣ በሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ወይም “በከፍተኛ ሁኔታ የሕዝብን ስርዓት የሚረብሹ ክስተቶች” ምክንያት ከቤታቸው እንደተፈናቀሉ ዘግቧል።

ይህን ቀውስ ማስወገድ የማንችለው እና ከባድ የሆነ ቀውስ ነው። ዛሬ ጠዋት፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በሲኒማ ዓለም ውስጥ የተሳተፉ ሰዎች “የዓለምን ቁስሎች መጋፈጥ” መፍራት እንደሌለባቸው አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል። ዓመፅ፣ ድህነት፣ ስደት፣ ብቸኝነት፣ ሱስ እና የተረሱ ጦርነቶች መታወቅ እና መተረክ ያለባቸው ጉዳዮች ናቸው” ሲሉ መናገራቸውን አስታውሰዋል።

አርቲስት ብላንቼት የሊቀ ጳጳሱን ንግግር ይህንን መልእክት በአእምሮው ይዘው እንደ ሚገኙ የገለጹ ሲሆን “ብዙውን ጊዜ ሰዎች በዕለት ተዕለት ሕይወታቸው ውስጥ ሊያፈሱት የማይችሉትን እንባ እያወሩ ነበር፣ ይህም ብዙውን ጊዜ በሲኒማ ውስጥ ይከሰታል፣ ወደ የዕለት ተዕለት ሥራችን እና እነዚያን የውይይት ክፍተቶች ለማነሳሳት እና ለመፍጠር” የቅዱስ አባታችን ጥሪ ተሰምቷቸዋል፣ ይህም በሲኒማ ውስጥ በሚገኙ የተስፋ ታሪኮች ሊጀምር ይችላል ሲሉ መናገራቸውም ተገልጿል።

17 Nov 2025, 15:30