2023.01.28 Gesù che predica sul monte 2023.01.28 Gesù che predica sul monte 

የየካቲት 15/2018 ዓ.ም የስደተኛው እለተ ሰንበት ንባባት እና የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ

የእለቱ ንባባት

1.      ሲራክ 15፡15-20

2.     መዝሙር 118

3.     1 ቆሮ. 2፡6-10

4.    ማቴ 5፡ 17-37

የእለቱ ቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ

ሕግና ነቢያት

ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ልሽር አልመጣሁም። እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ ከሕግ አንዲት ኢዮታ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም። ከእነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንድዋን እንኳ ችላ የሚል ሰዎችንም እንዲሁ የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ ነገር ግን የሚፈጽመው እንዲሁም የሚያስተምር ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል። ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም እላችኋለሁ።

ስለ ቁጣ የተሰጠ ትምህርት

“ለቀደሙት ‘አትግደል፥ የገደለ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል’ እንደተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ወንድሙን የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤ ወንድሙን ‘የማያስብ’ የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ‘ደደብ’ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል። መባህን በመሠዊያው ላይ በምታቀርብበት ጊዜ፥ በዚያ ሳለህ ቅር የተሰኘብህ ወንድም እንዳለ ብታስታውስ፥ መባህን እዚያው በመሠዊያው ፊት ትተህ ሂድ፤ አስቀድመህ ከወንድምህ ጋር ታረቅ፥ ከዚያ በኋላ መጥተህ መባህን አቅርብ። ባላጋራህ ለዳኛ፥ ዳኛውም ለሎሌው እንዳይሰጥህ ወደ እስር ቤት እንዳትገባ፤ ከባላጋራህ ጋር በመንገድ አብረኸው ስትሄድ ሳለህ ፈጥነህ ተስማማ፤ እውነት እልሃለሁ፥ የመጨረሻዋን ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከቶ ከዚያ አትወጣም።”

ስለማመንዘር የተሰጠ ትምህርት

“‘አታመንዝር’ እንደተባለ ሰምታችኋል። 28እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ወደ ሴት አይቶ የተመኛት ሁሉ ከወዲሁ በልቡ ከእርሷ ጋር አመንዝሮአል። ቀኝ ዐይንህ ብታሰናክልህ ከአንተ አውጥተህ ጣላት፤ ሰውነትህ በሙሉ ወደ ገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከሰውነትህ አንዱ ክፍል ቢጠፋ ይሻልሃልና። ቀኝ እጅህም ብታሰናክልህ ከአንተ ቆርጠህ ጣላት፤ ሰውነትህ በሙሉ ወደ ገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከሰውነትህ አንዱ ክፍል ቢጠፋ ይሻልሃልና።

ስለ መፋታት የተሰጠ ትምህርት

“‘ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ የፍቺ ወረቀት ጽሕፈት ይስጣት’ ተብሏል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በዝሙት ምክንያት ካልሆነ በስተቀር ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ አመንዝራ ያደርጋታል፤ የተፈታችውንም የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል።

ስለ መሐላ የተሰጠ ትምህርት

“ደግሞም ለቀደሙት ‘በውሸት አትማል ነገር ግን የማልኸውንም ለጌታ ስጥ’ እንደተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፤ በፍጹም አትማሉ፤ በሰማይ አትማሉ የእግዚአብሔር ዙፋን ነውና፤ በምድርም አትማሉ የእግሩ ማረፊያ ናትና፤ በኢየሩሳሌምም አትማሉ የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና፤ በራስህም አትማል፤ አንዲቱን ጠጉር እንኳ ነጭ ወይም ጥቁር ልታደርግ አትችልምና። ስለዚህ ንግግራችሁ አዎን አዎን ወይም አይደለም አይደለም ይሁን፤ ከእነዚህ የተረፈ ግን ከክፉው ነው።

የእለቱ ቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እሕቶቼ እንደምን አረፈዳቹ!

በዛሬው ስርዓተ አምልኮ በተነበበልን ቅዱስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ እንዲህ ብሏል:- “እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ። ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም” (ማቴ 5፡17)። ለመፈጸም፡ ይህ ኢየሱስንና መልእክቱን ለመረዳት ቁልፍ የሆነ ቃል ነው። ነገር ግን ይህ “ለመፈጸም” የሚለው ቃል ምን ማለት ነው? ይህን ለማስረዳት ያህል ጌታ የሚጀምረው ፍጻሜ ያላገኘውን ነገር በመናገር ነው። መጽሐፍ ቅዱስ  “አትግደል” ይላል፣ ነገር ግን ወንድሞች በቃላት ሊጎዱ ስለሚችሉ ይህ ቃል በቂ አይደለም ወይም ገና ሙሉ በሙሉ አልተሟላም። መጽሐፍ ቅዱስ “በሐሰት አትመስክር” ይላል፣ ነገር ግን አንድ ሰው በግብዝነት የሚሠራ ከሆነ መሃላ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም (ማቴ. 5፡21-37)። ይህ ምልአት አይደለም።

አንድ ተጨባጭ ምሳሌ ለመስጠት ያህል ኢየሱስ ትኩረቱን ያደረገው “ራስን መስዋዕት የማድረግ ሥነ ሥርዓት” ላይ ነው። ለእግዚአብሔር መስዋዕት ማቅረቡ የስጦታዎቹን ትርፍ ያስገኛል ። በጣም አስፈላጊ ሥነ ሥርዓት ነው - በምሳሌያዊ ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት መስዋዕት ማድረግ ፣ ቅን እንሁን ፣ ስጦታዎቹ ያለምክንያት ለእኛ መሰጠት - በጣም አስፈላጊ በመሆኑ ማቋረጥ በከባድ ምክንያቶች የተመሳ የተከለከለ ነው። ነገር ግን ኢየሱስ እንደ ተናገረው ከሆነ አንድ ሰው ወደ ጸሎት ከመሄዱ በፊት ወይም መስዋዕት ከመሰዋቱ በፊት አስቀድሞ ሄዶ በደል የፈጸመበት ወንድም ካለ ከእርሱ ጋር መታረቅ እንዳለበት ተናግሯል  (ማቴ 5፡23-24)። በዚህ መንገድ ብቻ የሥርዓቱ ፍጻሜ ይሆናል። መልእክቱ ግልጽ ነው፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ይወደናል፣ ምንም እንኳን እኛ የሚገባን ባንሆንም እንኳን በነጻነት፣ የመጀመሪያውን እርምጃ በወውሰድ እኛን ልጆቹን ወደ እርሱ በማቅረብ እንደሚወደን የሚነግረን ሲሆን እናም እኛ በተራችን ከበደሉን ሰዎች ጋር እርቅ ለማድረግ የመጀመሪያውን እርምጃ ሳንወስድ ፍቅሩን ማክበር አንችልም። በዚህ መንገድ በእግዚአብሔር ዓይን ውስጥ ሙላት ያለው ሰው እንሆናለን ማለት ነው፣ አለበለዚያ ውጫዊ የሆነ፣ ሙሉ በሙሉ የአምልኮ ሥርዓት መከበር ትርጉም የለሽ ነው፣ አስመሳይነት ይሆናል ማለት ነው።  በሌላ አነጋገር ኢየሱስ ሃይማኖታዊ ሕጎች አስፈላጊ መሆናቸውን እንድንገነዘብ ያደርገናል እነሱ ጥሩ ናቸው፥ ነገር ግን እነሱ ጅምር ብቻ ናቸው፣ እነሱን ለማሟላት ከጹሑፉ ባሻገር መሄድ እና ትርጉማቸውን መኖር አስፈላጊ ነው። እግዚአብሔር የሰጠን ትእዛዛት አየር በሌለበት መደበኛ የአምልኮ ሥርዓት ውስጥ መቆለፍ የለባቸውም። ያለበለዚያ "የእግዚአብሔር አብ" ልጆች ከመሆን ይልቅ "የእግዚአብሔር መምህሩ" አገልጋዮች ለሆኑት በውጫዊ ሃይማኖት ተከታዮች ተወስነናል ማለት ነው። ኢየሱስ የሚፈልገው እግዚአብሔርን እንደ መምህር ወይም ጌታ አድርገን እንድንመለከተው ብቻ ሳይሆን ነገር ግን እንደ አባት አድርገን ተመልክተን እንድንኖር ነው፣ ለእዚህም ነው ከጹሑፉ ባሻገር መሄድ አስፈላጊ የሆነው።

ወንድሞቼ እና እህቶቼ ይህ ችግር በኢየሱስ ጊዜ ብቻ አልነበረም፥ ዛሬም ቢሆን በእኛ ዘመን በሰፊው ይታያል። አንዳንድ ጊዜ ለምሳሌ “አባቴ ሆይ፣ አልገደልኩም፣ አልሰረኩም፣ ማንንም አልጎዳሁም…” በማለት እኔ ከሁሉም ነገር “የነፃው ነኝ” ለማለት በሚመስል መልኩ ራሳችንን ነፃ ለማድረግ እንሞክራለን። ይህ ደንቡን የጠበቀ ተዕዛዝ ነው፥ እሱም ተአዝዞን በትንሹ የሚገልጽ ነው፣ ኢየሱስ የሚፈልገው ግን የቻልነውን ያህል መሥራት እንድንመኝ ይጋብዘናል። ማለትም፡ እግዚአብሔር በሒሳብና በገበታ አያመዘንም፣ እንደአፍቃሪ አባት ሆኖ ይወደናል፡ በትንሹ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ! “እስከ የተወሰነ ነጥብ እወድሃለሁ” አይልም። እንደዚህ አያደርግም፣ እውነተኛ ፍቅር እስከ አንድ ነጥብ ድረስ ብቻ የተወሰነ ፈጽሞ አይደለም፣ እናም ፈጽሞ አይረካም፣ ፍቅር ሁል ጊዜ ከእዚያ ይሻገራል፣ አንድ ሰው ያለሱ ማድረግ አይችልም። ይህንንም ጌታ በመስቀል ላይ ነፍሱን አሳልፎ በመስጠት እና ገዳዮቹን ይቅር በማለት አሳይቶናል (ሉቃ. 23፡34)። እርሱ ደግሞ እርሱ እንደወደደን እርስ በርሳችን እንድንዋደድ በእርሱ ዘንድ እጅግ የተወደደውን ትእዛዝ በአደራ ሰጠን (ዮሐ. 15፡12)። ይህ ለህግ፣ ለእምነት፣ ለእውነተኛ ህይወት ፍጻሜ የሚሰጥ ፍቅር ነው!

ስለዚህ ወንድሞች እና እህቶች እንዴት እምነቴን ልኑር ብለን ራሳችንን እንጠይቅ ይሆናል? የሒሳብ ጉዳይ፣ የሥርዓተ-አምልኮ ጉዳይ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ያለ የፍቅር ታሪክ እንዴት ነ? ጉዳት ባለማድረግ ብቻ ረክቻለሁ፣ “ተግባሬን እና ሥራዬን ብቻ” በጥሩ ሁኔታ በመያዝ ወይም ለአምላክና ለሌሎች ያለኝን ፍቅር ለማሳደግ ጥረት አደርጋለሁ? እናም ሁል ጊዜ፣ በኢየሱስ ታላቅ ትእዛዝ እራሴን እፈትሻለሁ፣ እሱ እንደሚወደኝ ባልንጀራዬን እወዳለሁ ወይ? ምክንያቱም ምናልባት እኛ በሌሎች ላይ ለመፍረድ እንቸኩላለን፥ እናም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዳለ እና መሐሪ መሆኑን እንረሳለን።

የእግዚአብሔርን ቃል በፍፁምነት የተከታተለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እመነታችን እና ፍቅራችን ፍጻሜ እንዲኖረው እርሷ በአማላጅነቷ ትርዳን።

 

 

21 Feb 2026, 21:38