ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ የአለም የምግብ ቀን እና ድርጅቱ የተመሰረተ 80 ኛ አመትን ለማክበር በሮም በሚገኘው ጽ/ቤት ንግግር ስያደርጉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ የአለም የምግብ ቀን እና ድርጅቱ የተመሰረተ 80 ኛ አመትን ለማክበር በሮም በሚገኘው ጽ/ቤት ንግግር ስያደርጉ  (@Vatican Media)

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ፡ ‘ረሃብን ማሸነፍ የሰላም መንገድ ነው’ ማለታቸው ተገለጸ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ የአለም የምግብ ቀን እና ድርጅቱ የተመሰረተ 80 ኛ አመትን ለማክበር በሮም የሚገኘውን የምግብ እና የእርሻ ድርጅት (FAO) ዋና መሥሪያ ቤት ጎብኝተዋል። ቅዱስነታቸው በወቅቱ ባስተላለፉት መልእክት የቅድስት መንበር ከተቋሙ ጋር ያላትን ቅርበት በማረጋገጥ ረሃብን እና የተመጣጠነ ምግብ እጦትን ለማስወገድ የጋራ አለም አቀፍ ቁርጠኝነትን ይጠይቃል ሲሉ ተናግረዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

በሮም ከተማ የሚገኘው የ FAO ዋና መስሪያ ቤት ዓለምን የሚወክል መሥርያ ቤት ነው። ረሃብን፣ የምግብ እጦትን እና የተመጣጠነ ምግብ እጦትን በዘላቂነት የማሸነፍ ተልዕኮው የእያንዳንዱን ሰው ክብር በማስጠበቅ ግጭት፣ የአየር ንብረት ቀውስ፣ የግዳጅ ስደት እና በሀብታሞች እና በድሆች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ ባለበት አለም በፍትህ እና በሰላም ስም የሰውን ልጅ ተጠቃሚ ለማድረግ የአለም ማህበረሰብ ያለውን በጎ ፈቃድ ላይ ጥርጣሬን የፈጠረ መሥሪያ ቤት ነው።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ ሐሙስ ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም ጥዋት የዓለም የምግብ ቀንን እና የድርጅቱን 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ለማክበር በ FAO ለተሰበሰቡት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የዓለም መሪዎች እና በጎ ፈቃድ አምባሳደሮች እና ታዳሚዎች ለተሰበሰቡ ንግግር ባደረጉበት ወቅት የተናገሩት  ይህንኑ ነው።

"እሴቶችን በማወጅ ብቻ ልንረካ አንችልም፤ እሴቶችን ልናጣምራቸው ይገባል" ሲሉ የታደሰ የሥነ ምግባር መሠረት እንዲኖረን ጥሪ አቅርበዋል፡- “ መፈክሮች ሰዎችን ከመከራ አያወጡም፤ ትርፍ ከማግበስበስ ይልቅ የሰውን ልጅ ክብር በማስቀደም የምግብ ዋስትና፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን እና ዘላቂ የገጠር ልማት ማረጋገጥ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

እ.ኤ.አ. በ1970 ዓ.ም ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጳውሎስ ስድስተኛ ጀምሮ የቀደሙት መሪዎችን ፈለግ በመከተል ቅድስት መንበር ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰጠችውን የረጅም ጊዜ ድጋፍ ለማደስ እና አለም አቀፉ ማህበረሰብ ረሃብን፣ የተመጣጠነ ምግብ እጦትን እና የምግብ እጥረትን ለማጥፋት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ለማሳሰብ አጋጣሚውን ከፍቶላቸዋል።

" በራብ የሚሰቃይ ወንድሜ ነው"

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ረሃብን መዋጋት “የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ሥራ ብቻ ሳይሆን ጥልቅ ሰብዓዊና ሥነ ምግባራዊ ግዴታ ነው” ብለዋል።

“በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎችን ማየት እንግዳ ነገር አይደለም” ብሏል። “በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች ሁሉ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ናቸው፣ እናም ሳንዘገይ ልንረዳቸው የግባል" ብለዋል።

የዓለም የምግብ ድርጅት (FAO) ከተመሰረተ ከሰማንያ ዓመታት በኋላ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በቂ ምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ እንደሌላቸው አስታውሰዋል።

“እነዚህን ክፋቶች ለማስወገድ የሁሉንም፣ መንግስታት፣ ተቋማት፣ ሲቪል ማህበረሰብ እና እያንዳንዱ ሰው አስተዋጾ ይጠይቃል” ብሏል።

የጋራ የሞራል ውድቀት

በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ላይ ከ673 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በረሃብ እና በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ ሲሆን  እናም 2.3 ቢሊየን የሚሆኑት ደግሞ የተመጣጠነ ምግብ እንደሌላቸው የሚያሳዩትን ወቅታዊ መረጃዎችን በመጥቀስ፣ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ እነዚህ ቁጥሮች ረቂቅ ሳይሆኑ “የተሰበረ ሕይወት እና እናቶች ልጆቻቸውን መመገብ የማይችሉ መሆናቸውን የምያሳዩ ናቸው” ብለዋል።

“ነፍስ የሌለበት ኢኮኖሚ” እና ሰፊውን ህዝብ ለመከራ የሚዳርገውን የሀብት ክፍፍል ሥርዓትን አውግዘዋል፣ ሐብት በበዛበት ዘመን የረሃብን ጸንቶ መኖር “የጋራ የሞራል ውድቀትና የታሪክ ጥፋት ነው” ሲሉ አውግዘዋል።

"ምግብ ፈጽሞ መሳሪያ መሆን የለበትም"

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ምግብን እንደገና ለጦርነት መሣሪያነት እያገለገለ መሆኑ በጥልቀት አሳስቧቸዋል፣ ይህንንም “ወንዶችን፣ ሴቶችን እና ሕፃናትን መሠረታዊ መብታቸውን ማለትም የመኖር መብትን የሚነፍግ ጨካኝ ስልት ነው” በማለት ጠርተውታል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ረሃብን እንደ የጦር ወንጀል ማውገዙን በማስታወስ “ይህ ስምምነት የደበዘዘ ይመስላል” ሲሉ በምሬት ተናግሯል። በረሃብ የሚሞቱትን ዝምታ “በሰው ልጅ ኅሊና ውስጥ ይጮኻል” በማለት ሁሉም አገሮች ቆራጥ እርምጃ እንዲወስዱ አሳስቧል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ "ረሃብ የሰው ልጅ እጣ ፈንታ ሳይሆን ውድቀት ነው" ብለዋል። "የሚፈታው ችግር ብቻ ሳይሆን ወደ ሰማይ የሚወጣ ጩኸት ነው" ሲሉ የድሆች ጩኸት ሁሌም ወደ እግዚአብሔር እንደሚደርስ አስታውሰዋል።

የፖለቲካ ሥነ ምግባራዊ እይታ

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ከእርሳቸው በፊት ለነበሩት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ውድ የሆነውን ፅንሰ-ሀሳብ በድጋሚ ማረጋገጥን ቸል አላሉትም ፣ ምግብን መጣል ማለት ሰዎችን መጣል ማለት እንደሆነ በማመልከት ይህ ጉዳይ ሊያበቃ እንደሚገባ በአጽኖት ገለጸዋል።

ቅዱስነታቸው ሌሎች በረሃብ ላይ እያሉ የምግብ ብክነትን አውግዘዋል፣ እና የዓለም መሪዎች “አወዛጋቢ ሐሳቦችን” እንዲያስቆሙ እና “ርህራሄያችንን ከሚያደበዝዝ ግዴለሽነት እንድንነቃ” አሳስበዋል።

"ውሃ ህይወት ነው፣ ውሃ ምግብ ነው"

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የዘንድሮውን የዓለም የምግብ ቀን ጭብጥ በመጥቀስ መልእክቱ - "ውሃ ሕይወት ነው፣ ውሃ ምግብ ነው። ማንም ከተጠቃሚነት ሊገለል አይገባውም" በማለት ሁሉም ሰዎች አንድ ላይ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

"መከፋፈል እና ግዴለሽነት በታየበት ጊዜ በትብብር ውስጥ አንድነት ጥሩ ነገር ብቻ ሳይሆን ግዴታ ነው" ብለዋል። "እጅ በመያያዝ ብቻ ወደፊት የምግብ ዋስትና መብት ሳይሆን መብት የሆነበትን ጊዜ መገንባት እንችላለን" ሲሉ በአጽኖት ገለጸዋል።

“የመዳን ጸጥተኛ መሐንዲሶች፣ መጀመሪያ ተስፋን የዘሩና የፍጥረት ጠንቃቃ መጋቢዎች” በማለት ለገለጿቸው ሴቶች ልዩ ክብር ሰጥቷል። የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ማድረጋቸውን በመገንዘብ “የፍትህ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የበለጠ ሰብዓዊና ዘላቂ የሆነ የምግብ ሥርዓት ዋስትና ነው” ብለዋል።

የባለብዙ ወገን ትብብርን ማደስ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ የድሆች ድምፅ በቀጥታ እንዲሰማ የብዙ ወገንተኝነት እና የአገሮች ውይይት አስፈላጊነት በድጋሚ አረጋግጠዋል። "በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውስጥ ያለ እያንዳንዱ ተዋንያን እንድናገለግል ለተጠራን ሰዎች እውነተኛ ፍላጎቶች ውጤታማ ምላሽ እንዲሰጥ የሚያስችል ራዕይ መገንባት አለብን" ብለዋል።

በተጨማሪም በዩክሬን፣ በጋዛ፣ በሄይቲ፣ በአፍጋኒስታን፣ በማሊ፣ በመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ በየመን እና በደቡብ ሱዳን በረሃብና በዓመፅ ለሚሰቃዩት ብዙ ሕዝቦች ልባዊ ጥሪ አቅርቧል፣ “ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ወደ ሌላ አቅጣጫ ማየት አይችልም” በማለት አጥብቆ ተናግሯል።

"የሚበሉትን ስጣቸው"

ቅዱሱ አባታችን ንግግራቸውን ሲያጠናቅቁ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ “የሚበሉትን ስጡአቸው” (ማር 6፡37) ያለውን ቃል ጠቅሷል። አክሎም ይህ የወንጌል ትእዛዝ “ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አንገብጋቢ ፈተና ሆኖ ቆይቷል” ብሏል።

“እግዚአብሔርን ለመለመን አትታክቱ፣” ሲሉ ንግግራቸውን የደመደሙት ቅዱስነታቸው “ፍትሕ እንዲሰፍን ድፍረት እና ጉልበት እንዲሰጠን፣ ሁልጊዜም በቅድስት መንበር እና በዓለም ዙሪያ እጅግ የተቸገሩትን ለማገልገል የተዘጋጀችውን የቅድስት መንበር እና የመላው ቤተክርስቲያን አጋርነት ላይ መተማመን ትችላለህ" ሲሉ ቅዱስነታቸው ከተናገሩ በኋላ ንግግራቸውን አጠናቀዋል።

 

17 Oct 2025, 15:38