ፈልግ

በቱርክ በቮልስዋገን አሬና  የተከናወነ መስዋዕተ ቅዳሴ በቱርክ በቮልስዋገን አሬና የተከናወነ መስዋዕተ ቅዳሴ   (@Vatican Media)

በኢስታንቡል በተከናወነው መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ የተለያዩ የአይማኖት ተቋማት ንግግር አድርገዋል!

ቅዳሜ ዕለት ሕዳር 20/2018 በኢስታንቡል በሚገኘው የቮልስዋገን አሬና በሊቀ ጳጳሱ ሊዮ 14ኛ መሪነት በተከናወነው መስዋዕተ ቅዳሴ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት ምእመናን ደስታቸውን ይጋራሉ እና ጉብኝታቸው ለሁሉም የሰላም እና የአንድነት መልእክት መሆኑን እምነታቸውን ይገልጻሉ።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በሕዳር 2018 የቦስፎረስ ሰርጥ የሚያቋርጡትን ሦስቱን ድልድዮች በስብከታቸው ላይ እንዳስታወሱት፣ ምእመናን አንድነትን እና ሰላምን የሚያበረታቱ ድልድዮችን በራሳቸው ሕይወት እንዲገነቡ እንዳበረታቱት፣ ቅዳሜ፣ ህዳር 2018 በኢስታንቡል በሚገኘው የቮልስዋገን አሬና ቅዳሴ ላይ በተሳተፉበት ወቅት ከተለያዩ አገራት እና የተለያዩ ሐይማኖት ተቋማት የተውጣጡ ሰዎች ድምፃቸውን ሲያሰሙ ነበር።

አቶ ካን ሳንካር ከተለያዩ ሃይማኖቶች የተውጣጡ 10 ሰዎችን ይዞ በዝግጅቱ ላይ ለመገኘት ከቱርክ ደቡባዊ ክፍል ለ2 ሰዓታት ተጉዟል። "እኛ ካቶሊክ፣ አርመናዊ፣ ኦርቶዶክስ፣ ሶሪያክ ነን… ሁላችንም ክርስቲያን ነን፣ አንድ ላይ በመሳተፋችን በጣም ደስተኞች ነን" ሲል አጉልቶ ገልጿል።

ከዚህ በፊት ከአንድ ቀን በፊት በኢዝኒክ የኒቂያ ጉባኤ 1,700ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ለማክበር ከሊቀ ጳጳስ ሊዮ፣ ፓትርያርክ ባርቶሎሜው ቀዳማዊ እና ከሌሎች የክርስቲያን ተወካዮች ጋር በቴሌቪዥን የጸሎት ሥነ ሥርዓቱን ተከታትለው እንደነበር አክለው ገልጿል።  አክሎም በቱርክ ውስጥ ላሉ ክርስቲያኖች "ልዩ እና ታሪካዊ" ጊዜ እንደሆነ ተናግረዋል።

የ32 እና የ17 ዓመት እድሜ ያላቸው ኒኮላስ እና የይጊት ቢልጌ፣ ሁለቱም በመስዋዕተ ቅዳሴው ላይ በጎ ፈቃደኞች ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ተመሳሳይ ስሜት እንደነበራቸው ገልጸዋል።

“ለመስዋዕተ ቅዳሴ እዚህ መድረስ፣ መመልከት እና መሄድ ያሳፍራል። ይህ ለእኛ በቱርክ ላሉ ክርስቲያኖች ታሪካዊ ወቅት ነው፣ ስለዚህ በፈቃደኝነት ለመሳተፍ እና ማህበረሰቡን ለመርዳት ወስነናል” ስትል ይጊት የተባለች የ23 አመት ግለሰብ ተናግራለች፣ ሁለቱም የጳጳሱ ጉዞ አርማ የተለጠፈባቸው ነጭ ኮፍያዎችን ለብሰው ከኒኮላስ አጠገብ ቆማ ነበር።

ሰላምን ለማስተዋወቅ የተደረገ ጉብኝት

ኒኮላስ ኢራናዊ እና ካቶሊክ ነው፣ ነገር ግን ለብዙ ዓመታት በቱርክ ይኖር ነበር። በመኪና 16 ሰዓት ርቀት ላይ ባለች ከተማ ውስጥ የትምህርት ቤት መምህር ሆኖ ይሰራል፣ ስለዚህ ለመገኘት ወደ ኢስታንቡል በአውሮፕላን ተሳፍሯል።

“ባለፉት ሁለት ምሽቶች በደስታዬ ምክንያት መተኛት አልቻልኩም” ሲል የተናገረ ሲሆን በነሐሴ ወር የወጣቶች ኢዮቤልዩ በዓል ላይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን እንዳየ ተናግሯል።

ለዪጊት የሊቀ ጳጳስ ሊዮ ጉብኝት በአንድ ቃል ሊጠቃለል ይችላል፡ ሰላም። “ዛሬ ስለ ሰላም የሚያወራው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ብቻ እንደሆኑ በእርግጥ እናስባለን” ሲትል አፅንዖት ሰጥታ ተናግራለች።

“ሌላው መልእክት ‘ፍቅር’ የሚለው ቃል ይሆናል” ሲል ኒኮላስ አፅንዖት ሰጥቶ የተናገረ ሲሆን “ጎረቤቶቻችንን መውደድ እንዳለብን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተሰጠ ትእዛዝ ነው፤ ቱርክ ደግሞ ከጎረቤቶቻችን ጋር እንዴት መኖር እንዳለብን ማወቅ ያለብን ማህበረሰብ ነው፤ ምክንያቱም የተለያየ እምነት ስላላቸው” ሲል ተናግሯል።

በአርሜኒያ ሐዋርያዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አባል የሆነችው እና ለመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የምትሠራው ታማር ካራሱ ማዮግሉ፣ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጉብኝት በእነዚህ አስቸጋሪ ጊዜያት የሰላም ጥሪን ይወክላል ያለች ሲሆን “ስሜታችንን ለመግለጽ ቃላት ማግኘት ከባድ ነው፣ ነገር ግን ይህንን ጉዞ በማድረጋቸው በጣም ደስተኞች ነን፤ ለሁሉም ክርስቲያኖች እና ለዓለም ስለ ሰላምና እርቅ በጣም ትልቅ መልእክት ነው” ስትል አክላ ገልጻለች።

አርብ ዕለት ሕዳር 19/2018 በመንፈስ ቅዱስ ካቴድራል በተደረገው የካቶሊክ ማህበረሰብ ስብሰባ ላይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን እንዳየቻቸው እና ስለ ኒቂያ ጉባኤ ስለተዘጋጀው የኢኩሜኒካል ሲምፖዚየም መጽሐፍ ሊሰጧት እንደቻሉ ተናግራለች።

ወንድሞችና እህቶች መሆን

በኢስታንቡል የምትማር የጊኒ የ23 ዓመቷ ካቶሊክ ሴሊን ጉያቮጉዊ፣ ከጊኒ የመጣች እና በሁሉም ቦታዎች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን በቱርክ ለመገናኘት ፈጽሞ እንዳልጠበቀች ተናግራለች። “የክርስትና መነሻ በከፊል በቱርክ እንደሆነ አውቃለሁ፣ ነገር ግን ዛሬ የብዙ ሙስሊም አገር ነች። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን በቱርክ ማየት ተስፋን ያመጣል” ስትል ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ጊዜ ለማሳለፍ ጓጉታለች።

ፖል እና ሲልቪ ያባስ በምትኩ ከፈረንሳይ በተለይ በሊቀ ጳጳሱ ጉብኝት ላይ ለመሳተፍ ወደ ቱርክ ተጉዘዋል።

ሲልቪ ከለዳዊት ስትሆን እስከ 10 ዓመቷ ድረስ በቱርክ ኖራለች። “ልዩ በረከት እየተቀበልን እንደሆነ ይሰማናል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በእርግጥ ተስፋን እና የሰላምና የፍቅር መልእክት ያመጣሉ” ብለዋል።

“በዓለም ላይ ባሉ አገሮች ሁሉ፣ ክርስቲያኖች ወይም ሙስሊሞች ወይም ሌላ ሃይማኖት ከሆንን፣ ሁላችንም ወንድማማቾችና እህቶች ነን። መላው ዓለም ይህንን እንዲያውቅ እፈልጋለሁ” ሲሉ መናገራቸውም ተዘግቧል።

 

01 Dec 2025, 14:47