ፈልግ

ር.ሊ.ጳ ሊዮ የእግዚአብሔር መንግሥት መምጣት መዘጋጀት አጣዳፊ ሂደት ነው አሉ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ዘወትር እሁድ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተንተርሰው የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ እንደምያደርጉ የሚታወቅ ሲሆን በዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በሕዳር 28/2018 ዓ.ም ባድረጉት የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ አሁን ያለንበት የስብከተ ገና ወቅት ለፍትሃዊው ዳኛ መልስ ለመስጠት እንድንዘጋጅ ተጠርተናል ማለታቸው የተገለጸ ሲሆን ለእግዚአብሔር መንግሥት መምጣት መዘጋጀት ምን ያህል አጣዳፊ እንደሆነ እና ከጻድቁ ዳኛ ከኢየሱስ ጋር ስለምንገናኝበት ሁኔታ አስተንትኖ ማድረጋቸው ተገልጿል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ቅዱስነታቸው በወቅቱ ያደረጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተናዋል፣ እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።

የተወደዳድችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ፣ መልካም እለተ ሰንበት ይሁንላችሁ!

የዚህ ሁለተኛ የስብከተ ገና ሳምንት (ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ታዳሚዎች የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ አሁን የለንበት ወቅት የስብከተ ገና ሳምንት 2ኛ እለተ ሰንበት ላይ እንገኛለን) እሑድ ቅዱስ ወንጌል የእግዚአብሔርን መንግሥት መምጣት ያስታውቀናል (ማቴ 3:1-12)። የኢየሱስ ሕዝባዊ አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት፣ መጥምቁ ዮሐንስ፣ አስቀድሞ ተከስቶ በቦታው ታየ። ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ!” እያለ ሰብኳል (ማቴ 3:1)።

በ“አባታችን” ሆይ በተሰኘው ጸሎት ውስጥ ኢየሱስ ራሱ እንዳስተማረን በየቀኑ “መንግሥትህ ትምጣ” እያልን እንጸልያለን። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ለእኛ ያዘጋጀልንን አዲስ ነገር እንመለከታለን፣ የታሪክ ሂደት በዚህ ዓለም ኃያላን ሰዎች የተጻፈ እንዳልሆነ እንገነዘባለን። እንግዲህ ሀሳባችንንና ጉልበታችንን ለእግዚአብሔር አገልግሎት እናውል፣ እሱም ሊገዛን ሳይሆን እኛን ነፃ ሊያወጣን መጥቶአል። ይህ “ወንጌል” ነው፣ በእውነት የሚያነሳሳንና የሚስበን እውነተኛ የምሥራች  ቃል ነው።

በእርግጥ በስብከቱ ውስጥ፣ የመጥምቁ የአነጋገር ቃና  ከባድ ነው። ያም ሆኖ፣ ሕዝቡ በጥሞና ያዳምጣሉ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሕይወትን በቁም ነገር እንዲመለከቱ፣ አሁን ያለውን ጊዜ ተጠቅመው ከሚፈርደው ጋር በሚገናኙበት ጊዜ ራሳቸውን ለማዘጋጀት የጠየቀውን ልመና በቃሉ ውስጥ ይሰማሉ።

ይህ መጥምቁ ዮሐንስ የእግዚአብሔር መንግሥት በኢየሱስ ክርስቶስ በትሕትናና በምሕረት እንዴት እንደሚገለጥ ይገረማል። ነቢዩ ኢሳይያስ ኢየሱስን ከቁጥቋጦ ጋር አነጻጽሮታል፤ የኃይል ወይም የጥፋት ምስል ሳይሆን የመወለድና የአዲስነት ምስል ነው። ከሞተ የዛፍ ግንድ በሚበቅልበት ቀንበጥ ላይ፣ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎቹን በቀስታ መንፈስ ይጀምራል (ኢሳ. 11:1-10)። እያንዳንዳችን በሕይወታችን ውስጥ የደረሰብንን ተመሳሳይ ድንገተኛ ነገር ማሰብ እንችላለን።

ይህም ቤተክርስቲያኗ ከስልሳ ዓመታት በፊት በተጠናቀቀው በሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ ውስጥ ያጋጠማት ክስተት ነው። ሁሉም ሰው ለመቀበልና ለማገልገል በጉጉት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስንጓዝ የሚታደስ ተሞክሮ ነው። መንግሥቱ ሲፈጸም፣ ደካማ ወይም ዳር የሚመስሉት ነገሮች ብቻ ሳይሆን፣ በሰው ልጅ አነጋገር የማይቻሉትም ነገሮች እንኳን ይፈጸማሉ። በነቢዩ በተሰጡት ምስሎች ውስጥ፡- “ተኩላ ከበግ ጠቦት ጋር ይኖራል፤ ነብርም ከፍየል ግልገል ጋር ይተኛል፤ ጥጃ፤ የአንበሳ ደቦልና የሰባ ከብት በአንድነት ይሰማራሉ፤ ትንሽ ልጅም ይመራቸዋል (ኢሳ. 11፡6)።

እህቶችና ወንድሞች፣ ዓለም ይህን ተስፋ ምን ያህል ያስፈልጋታል! ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም። ለመንግሥቱ ራሳችንን እናዘጋጅ፣ እንቀበለው። ትንሹ ልጅ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይመራናል! ከተወለደበት ምሽት ጀምሮ እስከ መስቀል ላይ እስከሞተበት ጨለማ ሰዓት ድረስ ራሱን በእጃችን ያስቀመጠዋል፣ እንደ ፀሐይ መውጣት በታሪካችን ላይ ያበራል። አዲስ ቀን ተጀምሯል፤ እንነሳና በብርሃኑ እንሂድ!

ይህ ስብከተ ገና ወቅት መንፈሳዊነት ነው፣ በጣም የሚያበራና ተቸባጭ ጊዜ ነው። የመንገድ መብራቶች፣ የአዲሱ ዓለም ቀረጻ የሆነውን ኢየሱስን ከተቀበልን እያንዳንዳችን ትንሽ ብርሃን መሆን እንደምንችል ያሳስቡናል። ይህንን እንዴት ማድረግ እንደምንችል ከእናታችን ማርያም እንማር፤ እሷም በመጠባበቅ ታማኝ ሆና የምትቀጥል የተስፋ እናታችን ናት።

07 Dec 2025, 23:49

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >