ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በታይላንድ-ካምቦዲያ ድንበር ላይ የሚፈጠሩ ግጭቶች እንዲቆሙ ጸለዩ
የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን
ቅዱስነታቸው ረቡዕ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ካደረጉት የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ በመቀጠል ለምዕመናን ባስተላለፉት ሳምንታዊ መልእክት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በታይላንድ እና በካምቦዲያ ድንበር ከክልሉ በሚወጡት ሪፖርቶች በመስማታቸው "ጥልቅ ሀዘናቸውን" ገልጸዋል።
"በታይላንድ እና በካምቦዲያ ድንበር ላይ ስለተቀሰቀሰው ግጭት ዜና ስሰማ በጣም ያሳዝነኛል። በሲቪሎች ላይ ጉዳት ደርሷል፣ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቤታቸው ወጥተው ለመሰደድ ተገደዋል። ለእነዚህ ውድ ህዝቦች ያለኝን ቅርበት በጸሎት እገልጻለሁ" ሲሉ ቅዱስነታቸው ተናግረዋል።
ይህ ጥቃት ለአስርት ዓመታት የዘለቀው የድንበር ውዝግብ የቅርብ ጊዜውን ግጭት ያመለክታል፣ በዚህ ውስጥ የተከራከሩ የግዛት ክፍሎች - በተለይም በባህላዊ ጠቀሜታ ባላቸው የቤተመቅደስ ቦታዎች ዙሪያ ያሉ አካባቢዎች - በየጊዜው በሁለቱ ሀገራት መካከል የተኩስ ልውውጥ እንዲቀሰቀስ አድርገዋል። ቀደም ሲል በግልግል እና በክልል ዲፕሎማሲ የተደረጉ ጥረቶች ድንበሩን ለማረጋጋት ቢሞክሩም፣ የተኩስ አቁም ጥረቶች ብዙውን ጊዜ ደካማ ሆነው የአካባቢው ማህበረሰቦች በተደጋጋሚ በተኩስ አፋፍ ላይ እንዲወድቁ አድርገዋል።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በወቅቱ ያደረጉትን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ መጨረሻ ላይ ንግግር ሲያደርጉ፣ ቅዱስ አባታችን የእነዚህ ውጥረቶች ተደጋጋሚነት አዝነው ተፋላሚ ወገኖች "ተኩስ ወዲያውኑ እንዲያቆሙ እና ውይይቱን እንዲቀጥሉ" ጠይቀዋል።
