ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቫቲካን የዛይድ የሰብአዊ ወንድማማችነት ሽልማት አዘጋጆችን ባነጋገሩበት ወቅት፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቫቲካን የዛይድ የሰብአዊ ወንድማማችነት ሽልማት አዘጋጆችን ባነጋገሩበት ወቅት፣  (@Vatican Media)

ር.ሊ.ጳ ሊዮ ለዛይድ የሽልማት አዘጋጆች፣ ቃላት ብቻ በቂ አይደሉም፣ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል አሉ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቫቲካን የዛይድ የሰብአዊ ወንድማማችነት ሽልማት አዘጋጆችን ባነጋገሩበት ወቅት፣ በመለያየት በሚታወቅ ዓለም ውስጥ የደግነት እና የበጎ አድራጎት ምስክር መሆን አስፈላጊ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፣ እንዲሁም ወንድማማችነትን ለማሳካት ተጨባጭ እርምጃዎችን አዘጋጆቹ መውሰድ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

በቫቲካን የዛይድ የሰብአዊ ወንድማማችነት ሽልማት አዘጋጆችን ባነጋገሩበት ወቅት፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቫቲካን ከተካሄደው የዛይድ የሰብአዊ ወንድማማችነት ሽልማት አዘጋጆች ጋር በመገናኘታቸው “ተሰጥኦአቸውን፣ ራዕያቸውን እና የሞራል እምነታቸውን ለሰብአዊ ወንድማማችነት ክቡር አገልግሎት ከሚያቀርቡት” ቡድን ጋር በመሆናቸው ደስታቸውን ገልጸዋል።

የዛይድ ሽልማት በዓለም ዙሪያ ያሉ ግለሰቦችን ወይም ድርጅቶችን ልዩነትን ለማጥበብ እና እውነተኛ የሰው ልጅ ግንኙነቶችን ለመገንባት የሚሠሩትን እውቅና የሚሰጥ ገለልተኛ እና ዓለም አቀፍ ሽልማት ሲሆን ብዙውን ጊዜ በግል መስዋዕትነት ለከፈሉ ግለሰቦች የሚሰጥ ሽልማት ነው።

በስብሰባው ላይ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የዛይድ ሽልማት መፈጠር የመነጨው በቀድሞ ርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ እና በታላቁ ኢማም አህመድ አል-ታዬብ በሰብአዊ ወንድማማችነት ሰነድ ላይ በመፈረማቸው እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተው የተናገሩት ቅዱስነታቸው ይህም በሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን የተደገፈ ሽልማት መሆኑንም ቅዱስነታቸው አስታውሰዋል። ቅዱስ አባታችን ሽልማቱ የሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን እና የሌሎች መሪዎችን ቅርስ እንደሚያካትት አብራርተዋል።

ከዚህም በላይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ የዛይድ ሽልማት “እያንዳንዱ ሰው እና እያንዳንዱ ሃይማኖት ወንድማማችነትን ለማስፋፋት የተጠራ መሆኑን አፅንዖት እንደሚሰጥ” አጉልተው ገልጸዋል። የተለያዩ የሃይማኖት ወጎች ወንድማማችነትን ለመገንባት ሊረዱ እንደሚችሉ የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ የተናገሩትን አስታውሰዋል።

በዓለም ላይ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በመገንዘብ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ “ሁላችንም ወንድማማች እና እህትማማች መሆናችንን ለማስታወስ የሰው ልጅ ደግነት እና የበጎ አድራጎት እውነተኛ ምስክርነት” እንዲሆኑ ሁሉንም ሰው ጠይቀዋል። ነገር ግን፣ “ቃላት በቂ አይደሉም” ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ተጨባጭ እርምጃዎችም መወሰድ አለባቸው ምክንያቱም ያለእነሱ፣ ምርጥ እና ተስፋ ሰጪ ግቦቻችን እንኳን “ይዳከማሉ እና ይጠፋሉ” ሲሉ ተናግረዋል።

የዛይድ ሽልማት “ርህራሄን እና አንድነትን ለማሳየት ተጨባጭ እርምጃዎችን የሚወስዱ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና ይሰጣል እና ያከብራል፣ ዛሬ የሰው ልጅ ወንድማማችነትን እንዴት ማሳደግ እንደምንችል ተጨባጭ ምሳሌዎችን ይሰጣል” ሲሉ ቅዱስነታቸው አክለው ገልጸዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ጸሎታቸውን ለአዘጋጆቹ በማረጋገጥ እና “ለሰው ልጅ ቤተሰብ ጥቅም” የሚያደርጉትን ቁርጠኛ ሥራ በማበረታታት ደምድመዋል።

12 Dec 2025, 15:39