ፈልግ

POPE-AFRICA/SOUTHSUDAN

የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን በተመለከተ አውሮፓ እና አፍሪካ ምላሽ ሰጡ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በሚመጡት ወራት ውስጥ ከሚጎበኟቸው የተለያዩ አገሮች ውስጥ ካሉ የሲቪል እና የቤተክርስቲያን ባለስልጣናት ምስጋና እና ጉጉት እየተገለጸ ይገኛል፣ ከሞናኮ፣ ከአልጄሪያ፣ ከካሜሩን፣ ከአንጎላ፣ ከኢኳቶሪያል ጊኒ እና ከስፔን።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በሚቀጥሉት ወራት ከሚጎበኟቸው የተለያዩ አገሮች፣ ጉዞዎቹ በተመለከተ የቅድስት መንበር የፕሬስ ጽሕፈት ቤት የካቲት 18/2018 ዓ.ም በይፋ ከገለጸ በኋላ፣ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ ሊጎበኟቸው ከሚችሏቸው የተለያዩ አገሮች በጎ ምላሾች እየወጡ ነው።

የመጀመሪያ ጉብኝታቸው እ.አ.አ መጋቢት 28/2026 በሞናኮ ይሆናል፤ ከዚያም እ.አ.አ ከሚያዝያ13 እስከ 23/2026 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ 11 ቀናት የሚፈጅ ጉዞ በማድረግ በአልጄሪያ፣ ካሜሩን፣ አንጎላ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ አቋርጦ እ.አ.አ ከሰኔ 6 እስከ 12/2026 ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ ስፔን ለአንድ ሳምንት የሚፈጅ ጉዞ ያደርጋሉ፣ ይህም ማድሪድ፣ ባርሴሎና፣ የካናሪ ደሴቶች፣ ቴነሪፍ እና ግራን ካናሪያን ያካትታል።

የቅድስት መንበር የፕሬስ ጽሕፈት ቤት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቅርቡ የሚደረጉትን ሐዋርያዊ ጉዞዎች አስታውቋል፡- በሚያዝያ ወር በአልጄሪያ፣ ካሜሩን፣ አንጎላ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ መካከል ለአስር ቀናት በአፍሪካ፤ ሐዋርያዊ ጉብኝት እንደምያደርጉ ይጠበቃል።

በአልጄሪያ፣ ጳጳሳቱ “እጅግ እንደተደሰቱ” ይናገራሉ፣ በካሜሮን ደግሞ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጉብኝት በፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ችግሮች መካከል “የተስፋ ምልክት” ተብሎ ይገለጻል፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ለስላሳ የሆነ ጉብኝት ለማረጋገጥ አስቀድሞ ዝግጅት እየተደረገ ነው።

ከስፔን “የደስታ” እና “የምስጋና ማዕበል” እየመጣ ይገኛል፣ እንዲሁም “ሞቅ ያለ” አቀባበል ማረጋገጫዎች እየተገለጹ ይገኛሉ። በሞናኮ ግዛት ውስጥም ተመሳሳይ ነገር አለ፣ የንጉሣዊ ቤተሰብም ሆነ የአካባቢው ቤተክርስቲያን የዚህን “ታሪካዊ ጊዜ” “ክብር” አፅንዖት የሚሰጡበት፡ ርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ትንሹ የከተማ-ግዛት የምያደርጉት የመጀመሪያ ጉብኝት ነው።

የሞናኮ ሊቀ ጳጳስ እና የልዑሉ ቤተ መንግሥት

ጉዞዎቹ ከተነገሩ በኋላ ወዲያውኑ በርካታ መግለጫዎች ተሰጥተዋል፣ ከሞናኮ ሊቀ ጳጳስ እና ከልዑሉ ቤተ መንግሥት የተውጣጡ መግለጫዎች በይፋ ተነግረዋል።

በርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት ማስታወሻ ላይ እ.አ.አ በ2027 ዓ.ም የሚከበሩ ሁለት መታሰቢያዎችን አስታውሰዋል፤ በሞናኮ ሮክ ላይ የመጀመሪያው ቁምስና የተመሰረተበት 780ኛ ዓመት ክብረ በዓል፣ በሊቀ ጳጳስ ኢኖሰንት አራተኛ ፊርማ በጸደቀ ይፋዊ ሰነድ "ፕሮ ፑሪታቴት" (እ.አ.አ ታህሳስ 6፣ 1247) የተቋቋመ ሲሆን፣ የሊቀ ጳጳስ ሊዮ 12ኛ ይፋዊ ሰነድ በላቲን ቋንቋ) "ኩማድሞደም ሶሊሲተስ ፓስተር" 140ኛ ዓመት ክብረ በዓል፣ የሞናኮ ሀገረ ስብከትን በቀጥታ ለቅድስት መንበር ተገዢ አድርጎታል።

“ወጣት ሀገረ ስብከት፣ ነገር ግን በታሪክ የበለፀገ የአካባቢ ቤተክርስቲያን፣ የሞናኮ ቤተክርስቲያን በሞንጋስክ ሕይወት ውስጥ ማዕከላዊ ተቋም ሆና ትቀጥላለች እና በብዙ መንገዶች ሕያው ናት፣ ብዙውን ጊዜ ለሕዝብ የማይታወቅ ነው” ሲል መግለጫው ይፋ አድርጓል።

በተጨማሪም በንጉሣዊው ቤተሰብ እና በቅዱስ ጴጥሮስ ተተኪዎች መካከል የነበረውን ለዘመናት የዘለቀ ትስስር እንዲሁም የሞናኮ ርዕሰ መስተዳድር “የካቶሊክ እምነት የመንግሥት ሃይማኖት ከሆነባቸው ጥቂት አገሮች አንዷ” መሆኗን በድጋሚ ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ “ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው ድረስ ለሰው ልጅ ሕይወት አክብሮት”፣ ለተቀናጀ ሥነ-ምህዳር መጨነቅ እና “የጋራ ቤታችንን” መጠበቅ እና ለስፖርት ያለን ፍቅር ያሉ በርካታ የጋራ ግዴታዎች አሉ።

እንደ ሊቀ ጳጳስ ዶሚኒክ-ማሪ ዴቪድ ገለጻ፣ እነዚህ ግንኙነቶች “ቀደም ሲል ኮምፓስ ወይም አቅጣጫ መጠቆምያ ሆነው ቆይተዋል እናም ውሳኔዎቻችንን መምራታቸውን ቀጥለዋል… ዛሬ፣ ዓለምን - እና እኛንም እንደሌሎች ሁሉ - ልዑል አልበርት ዳግማዊ የሁሉንም ሰው ሕሊና ለመሳብ እና የእያንዳንዱን ሰው የኃላፊነት ስሜት ሕያው ለማድረግ ሁሉንም ጥረት እናደርጋለን" ብለዋል። ልዑል አልበርት ዳግማዊ ራሳቸው - እ.አ.አ በጥር 17 በሊቀ ጳጳስ ሊዮ 14ኛ - ከልዕልት ቻርሌን ጋር በመሆን የተቀበሉት፣ የጳጳሱ ጉብኝት "የግሪማልዲ ሥርወ መንግሥትን ከጴጥሮስ ተተኪዎች ጋር ከሚያገናኙት ለዘመናት የዘለቀ ግንኙነት ቀጣይነት ጋር የሚጣጣም እንዲሁም በሞናኮ ርዕሰ መስተዳድር እና በቅድስት መንበር መካከል ባለው ረጅም ጊዜ የዘለቀ እና እምነት የሚጣልበት የዲፕሎማሲ ግንኙነት ማዕቀፍ ውስጥ የሚስማማ ነው" ብለዋል።

ከቤተ መንግሥቱ የወጣው መግለጫ ይህ "ድርብ ጠቀሜታ ያለው፣ ተቋማዊም ሆነ ሐዋርያዊ" የሆነ ክስተት መሆኑን እና "በውይይት፣ በሰላም እና በጋራ ኃላፊነት መንፈስ ጠንካራ የተስፋ ምልክት" እንደሚሆን አፅንዖት ሰጥቶ ገልጿል።

የአልጄሪያ ጳጳሳት፡ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ፣ “የሰላም ሐዋርያ”

የአልጄሪያ ጳጳሳት ተስፋ፣ ውይይት እና ሰላም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ አልጀርስ እና አናባ የምያደርጉትን ጉብኝት በተመለከተ የሚያጎሉባቸው ቁልፍ ጭብጦች ናቸው።

ጉዞው የሊቀ ጳጳሱ ማሕበር አባል፣ የሃይማኖት ሥርዓት መንፈሳዊ አባት የሆነውን የቅዱስ አውጉስጢኖስ ፈለግ ይከተላል። በታህሳስ ወር በሊባኖስ ከነበራቸው ጉብኝት ሲመለሱ በበረራ ላይ በነበሩበት ወቅት በጋዜጣዊ መግለጫቸው “የቅዱስ አውጉስጢኖስን ቦታዎች ለመጎብኘት ወደ አልጄሪያ ለመሄድ እንዲሁም በክርስቲያን ዓለም እና በሙስሊሙ ዓለም መካከል ያለውን ውይይት እና ድልድዮችን ለመገንባት ተስፋ አደርጋለሁ” ሲሉ ይህንን ጉዞ አስቀድመው ገልጸው ነበር።

ርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ከሊባኖስ ወደ ሮም በሚመለሱት ወቅት የሊቀ ጳጳሳት አውሮፕላን ውስጥ ተሳፍረው ሳለ በሰላም ድርድር ውስጥ “ከትዕይንቱ በስተጀርባ” ስለሚሠራው የቅድስት መንበር ሚና ለጋዜጠኞች መናገራቸው ይታወሳል።  ቀኑ የተወሰነ ስለሆነ የአልጄሪያ ጳጳሳት፣ ከካርዲናል ዣን ፖል ቬስኮ ጋር፣ ይህን  ጉብኝት በጉጉት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ “የአልጄሪያን ሕዝብና መሪዎቻቸውን ለመገናኘት ይመጣሉ”፣ እንዲሁም “ቤተክርስቲያናችንን በብዛት ሙስሊም ሕዝብ መካከል የወንድማማችነት መገኘት ተልዕኮዋን እንድታሳድግ ለማበረታታት” እንዲሁም “በዚህች ምድር የተወለደ አንድ የጋራ ሽማግሌ ወንድም በቅዱስ አውጉስጢኖስ ማንነት መኖሩ ያስገኘልንን በረከት ለማስታወስ ይመጣሉ፣ ምሳሌውም የጋራ መንገዳችንን ሊመራ ይችላል” ሲሉ ተናግረዋል።

እንደ ጳጳሳቱ ገለጻ፣ የቲቢሪን መነኮሳት ሰማዕትነት የተከናወነበትን አገር በመጎብኘት - እንደ “የሰላም ሐዋርያ”፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የክርስቶስን መልእክት እና ማበረታቻ “ከቀደመውም ሆነ ከአሁኑ፣ ከተለዋዋጭ ግንኙነቶች ወይም አለመግባባቶች ባሻገር፣ ከሁሉም በላይ በሰላም አብረን ለመኖር በቅን ልቦና ፍላጎት ልንሞላ እንችላለን” ብለዋል። ስለዚህም ምእመናን ለዚህ ጉብኝት “በልባችንና በማህበረሰባችን ውስጥ፣ ከጓደኞቻችን ጋር በመነጋገር” በጸሎት እንዲዘጋጁ ይጠይቃሉ።

በካሜሩን ተስፋዎችና ግምቶች

“ቀጣይነት ባለው የፖለቲካና የደህንነት ፈተናዎች አውድ ውስጥ”፣ የጳጳሱ ወደ ካሜሩን የሚያደርጉት ጉብኝት በቤተክርስቲያኒቱም ሆነ በአካባቢው ህዝብ “የተስፋ ምልክት” ተደርጎ ይታያል። በየካቲት 18/2018 ዓ.ም በካሜሮን የቅድስት መንበር ልዑክ የሆኑት አቡነ ኤቭሊኖ ቤትንኮርት ይፋ የተደረገው መግለጫ በካሜሮናዊያን መካከል “ከፍተኛ ጉጉት እና ክርክር አስነስቷል” ሲል የባሜንዳ ሊቀ ጳጳሳት መግለጫ ያስረዳል።

ይህ መግለጫ ባለስልጣናት ለሳምንታት የመሠረተ ልማትን ለማሻሻል ሲሰሩ እንደነበር ያጎላል። ይህም “የካሜሩንን ካቶሊኮች እምነት ለማጠናከር፣ ሰላምን ለማስፈን እና የአገሪቱን የሰብአዊ ቀውስ ለመፍታት ትኩረት መስጠት” ያለበት ጉብኝት ስኬታማ እንዲሆን ያደርጋል ብለዋል።

የስፔን የአደረጃጀት ማሽን ቀድሞውኑ በእንቅስቃሴ ላይ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የቅድስት መንበር የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጉብኝት በመጪው ሰኔ ወር እንደሚደረግ ይፋ ከተደረገ በኋላ የማድሪድ ሊቀ ጳጳሳት ደስታቸውን ገልጸዋል። መላው የሀገረ ስብከት ማህበረሰብ ዜናውን “ለማድሪድ ቤተክርስቲያን የተስፋ እና የኅብረት ምንጭ” አድርጎ ይመለከተዋል ሲል የጳጳሳት ጉባኤ መግለጫ ገልጿል።

ለወራት የስፔን ዋና ከተማ “ሰፊ እና ውስብስብ ሥራ” የሆነውን ነገር ለማደራጀት ስትሰራ ቆይታለች፣ በተለይም ስፔን ለመጨረሻ ጊዜ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትን ከተቀበለች 14 ዓመታት ያህል ሆኗታል፣ - ቤኔዲክት 16ኛ እ.አ.አ በ2011ዓ.ም የዓለም ወጣቶች ቀንን ለመጎብኘት በሄዱበት ወቅት ከተደረገ ጉብኝት ውጪ ሌላ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ደረጃ የተከናወነ ሐዋርያዊ ግብኝት ለአለፉት 14 አመታት አለተከናወነም።

ዝግጅቱ “የብዙ ሰዎች እና የቤተክርስቲያን አካላት ቅንጅት፣ እቅድ ማውጣት እና ትብብር” ይጠይቃል። ስለዚህ የማድሪድ ሊቀ ጳጳስ ለረጅም ጊዜ አስፈላጊውን የድርጅታዊ መዋቅር አዘጋጅተዋል፣ እና ካርዲናል ሊቀ ጳጳስ ሆሴ ኮቦ ካኖ የተለያዩ የሐዋርያዊ እንክባካቤ እና የሎጂስቲክስ ገጽታዎችን እያስተዳደረ ያለ የሀገረ ስብከት ኮሚሽን አቋቁመዋል።

ማድሪድም እንዲሁ በደብር፣ በማህበረሰቦች፣ በእንቅስቃሴዎች እና በትምህርት ማዕከላት ውስጥ “መንፈሳዊ ዝግጅት” እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። ጸሎት እና ክፍት ልብ፣ “የቅዱስ አባታችን መገኘት በእምነት፣ በአንድነት እና በሚስዮናዊነት እድሳት ፍሬ እንደሚያፈራ ተስፋ በማድረግ” እየተጠባበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም በስፔን የጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሊቀ ጳጳስ ሉዊስ አርጉኤሎ ጉብኝቱ “የልብ ክፍትነት” እና “አደረጃጀት” አንፃር “ፈተና” እንደሆነ አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

ሊቀ ጳጳስ ሉዊስ አርጉኤሎ አክለውም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ “ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን በቤተክርስቲያኒቱ እምነት ውስጥ ለማፅናት ስፔንን እንደሚጎበኙ አክለውም የገለጹ ሲሆን ይህ እምነት በቤተክርስቲያናችን ተጨባጭ ሕይወት ውስጥ ወደ ተስፋና ቸርነት እንደሚለወጥ” ተናግረዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የባርሴሎና ሊቀ ጳጳስ እና የሳግራዳ ፋሚሊያ የግንባታ ኮሚቴ ባዚሊካውን ለመጎብኘት የቀረበላቸውን ግብዣ በመቀበል በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ የ“አመስጋኝነት” መንፈስ እንዳላቸው ገልጸዋል፣ የህንፃው ጀማሪ አንቶኒ ጋውዲ የሞት 100ኛ ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይም ቤኔዲክቶስ 16ኛ እ.አ.አ በ2010 ዓ.ም የካታላን ከተማን የጎበኙት የመጨረሻው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሲሆኑ፣ የሳግራዳ ፋሚሊያን የመቀደስ ሥነ ሥርዓት በመሩበት ወቅት ነበር።

ማንነቷ በክርስትና እምነት የተቀረጸ ቢሆንም፣ በዓለማዊነትም የተጎዳች ወደሆነች ትልቅ የአውሮፓ አገር፣ ስፔን። በመጨረሻም፣ ቅዱስ አባታችን በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን በማቋረጥ እና ማረፊያዎችን በማድረግ ከአፍሪካ ወደ አውሮፓ ከሚደረጉ ዋና ዋና የስደተኞች መንገዶች አንዱ በሆነው በካናሪ ደሴቶች ሐዋርያዊ ጉዞውን ያጠናቅቃሉ።

26 Feb 2026, 13:18