ፈልግ

ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ እምነት ከእግዚአብሔር ጋር ያለ የፍቅር ታሪክ ነው ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ዘወትር እሁድ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተንተርሰው የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ እንድምያደርጉ የሚይታወቅ ሲሆን በዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በየካቲት 05/2015 ዓ.ም ባደርጉት አስተንትኖ እምነት ከእግዚአብሔር ጋር ያለ የፍቅር ታሪክ ነው ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራብ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ቅዱስነታቸው በወቅቱ ያደርጉትን አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው አሰናድተነዋል እንድትከተታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እሕቶቼ እንደምን አረፈዳቹ!

በዛሬው ስርዓተ አምልኮ በተነበበልን ቅዱስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ እንዲህ ብሏል:- “እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ። ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም” (ማቴ 5፡17)። ለመፈጸም፡ ይህ ኢየሱስንና መልእክቱን ለመረዳት ቁልፍ የሆነ ቃል ነው። ነገር ግን ይህ “ለመፈጸም” የሚለው ቃል ምን ማለት ነው? ይህን ለማስረዳት ያህል ጌታ የሚጀምረው ፍጻሜ ያላገኘውን ነገር በመናገር ነው። መጽሐፍ ቅዱስ  “አትግደል” ይላል፣ ነገር ግን ወንድሞች በቃላት ሊጎዱ ስለሚችሉ ይህ ቃል በቂ አይደለም ወይም ገና ሙሉ በሙሉ አልተሟላም። መጽሐፍ ቅዱስ “በሐሰት አትመስክር” ይላል፣ ነገር ግን አንድ ሰው በግብዝነት የሚሠራ ከሆነ መሃላ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም (ማቴ. 5፡21-37)። ይህ ሙላት አይደለም።

አንድ ተጨባጭ ምሳሌ ለመስጠት ያህል ኢየሱስ ትኩረቱን ያደረገው “ራስን መስዋዕት የማድረግ ሥነ ሥርዓት” ላይ ነው። ለእግዚአብሔር መስዋዕት ማቅረቡ የስጦታዎቹን ትርፍ ያስገኛል ። በጣም አስፈላጊ ሥነ ሥርዓት ነው - በምሳሌያዊ ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት መስዋዕት ማድረግ ፣ ቅን እንሁን ፣ ስጦታዎቹ ያለምክንያት ለእኛ መሰጠት - በጣም አስፈላጊ በመሆኑ ማቋረጥ በከባድ ምክንያቶች የተመሳ የተከለከለ ነው። ነገር ግን ኢየሱስ እንደ ተናገረው ከሆነ አንድ ሰው ወደ ጸሎት ከመሄዱ በፊት ወይም መስዋዕት ከመሰዋቱ በፊት አስቀድሞ ሄዶ በደል የፈጸመበት ወንድም ካለ ከእርሱ ጋር መታረቅ እንዳለበት ተናግሯል  (ማቴ 5፡23-24)። በዚህ መንገድ ብቻ የሥርዓቱ ፍጻሜ ይሆናል። መልእክቱ ግልጽ ነው፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ይወደናል፣ ምንም እንኳን እኛ የሚገባን ባንሆንም እንኳን በነጻነት፣ የመጀመሪያውን እርምጃ በወውሰድ እኛን ልጆቹን ወደ እርሱ በማቅረብ እንደሚወደን የሚነግረን ሲሆን እናም እኛ በተራችን ከበደሉን ሰዎች ጋር እርቅ ለማድረግ የመጀመሪያውን እርምጃ ሳንወስድ ፍቅሩን ማክበር አንችልም። በዚህ መንገድ በእግዚአብሔር ዓይን ውስጥ ሙላት ያለው ሰው እንሆናለን ማለት ነው፣ አለበለዚያ ውጫዊ የሆነ፣ ሙሉ በሙሉ የአምልኮ ሥርዓት መከበር ትርጉም የለሽ ነው፣ አስመሳይነት ይሆናል ማለት ነው።  በሌላ አነጋገር ኢየሱስ ሃይማኖታዊ ሕጎች አስፈላጊ መሆናቸውን እንድንገነዘብ ያደርገናል እነሱ ጥሩ ናቸው፥ ነገር ግን እነሱ ጅምር ብቻ ናቸው፣ እነሱን ለማሟላት ከጹሑፉ ባሻገር መሄድ እና ትርጉማቸውን መኖር አስፈላጊ ነው። እግዚአብሔር የሰጠን ትእዛዛት አየር በሌለበት መደበኛ የአምልኮ ሥርዓት ውስጥ መቆለፍ የለባቸውም። ያለበለዚያ "የእግዚአብሔር አብ" ልጆች ከመሆን ይልቅ "የእግዚአብሔር መምህሩ" አገልጋዮች ለሆኑት በውጫዊ ሃይማኖት ተከታዮች ተወስነናል ማለት ነው። ኢየሱስ የሚፈልገው እግዚአብሔርን እንደ መምህር ወይም ጌታ አድርገን እንድንመለከተው ብቻ ሳይሆን ነገር ግን እንደ አባት አድርገን ተመልክተን እንድንኖር ነው፣ ለእዚህም ነው ከጹሑፉ ባሻገር መሄድ አስፈላጊ የሆነው።

ወንድሞቼ እና እህቶቼ ይህ ችግር በኢየሱስ ጊዜ ብቻ አልነበረም፥ ዛሬም ቢሆን በእኛ ዘመን በሰፊው ይታያል። አንዳንድ ጊዜ ለምሳሌ “አባቴ ሆይ፣ አልገደልኩም፣ አልሰረኩም፣ ማንንም አልጎዳሁም…” በማለት እኔ ከሁሉም ነገር “የነፃው ነኝ” ለማለት በሚመስል መልኩ ራሳችንን ነፃ ለማድረግ እንሞክራለን። ይህ ደንቡን የጠበቀ ተዕዛዝ ነው፥ እሱም ተአዝዞን በትንሹ የሚገልጽ ነው፣ ኢየሱስ የሚፈልገው ግን የቻልነውን ያህል መሥራት እንድንመኝ ይጋብዘናል። ማለትም፡ እግዚአብሔር በሒሳብና በገበታ አያመዘንም፣ እንደአፍቃሪ አባት ሆኖ ይወደናል፡ በትንሹ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ! “እስከ የተወሰነ ነጥብ እወድሃለሁ” አይልም። እንደዚህ አያደርግም፣ እውነተኛ ፍቅር እስከ አንድ ነጥብ ድረስ ብቻ የተወሰነ ፈጽሞ አይደለም፣ እናም ፈጽሞ አይረካም፣ ፍቅር ሁል ጊዜ ከእዚያ ይሻገራል፣ አንድ ሰው ያለሱ ማድረግ አይችልም። ይህንንም ጌታ በመስቀል ላይ ነፍሱን አሳልፎ በመስጠት እና ገዳዮቹን ይቅር በማለት አሳይቶናል (ሉቃ. 23፡34)። እርሱ ደግሞ እርሱ እንደወደደን እርስ በርሳችን እንድንዋደድ በእርሱ ዘንድ እጅግ የተወደደውን ትእዛዝ በአደራ ሰጠን (ዮሐ. 15፡12)። ይህ ለህግ፣ ለእምነት፣ ለእውነተኛ ህይወት ፍጻሜ የሚሰጥ ፍቅር ነው!

ስለዚህ ወንድሞች እና እህቶች እንዴት እምነቴን ልኑር ብለን ራሳችንን እንጠይቅ ይሆናል? የሒሳብ ጉዳይ፣ የሥርዓተ-አምልኮ ጉዳይ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ያለ የፍቅር ታሪክ እንዴት ነ? ጉዳት ባለማድረግ ብቻ ረክቻለሁ፣ “ተግባሬን እና ሥራዬን ብቻ” በጥሩ ሁኔታ በመያዝ ወይም ለአምላክና ለሌሎች ያለኝን ፍቅር ለማሳደግ ጥረት አደርጋለሁ? እናም ሁል ጊዜ፣ በኢየሱስ ታላቅ ትእዛዝ እራሴን እፈትሻለሁ፣ እሱ እንደሚወደኝ ባልንጀራዬን እወዳለሁ ወይ? ምክንያቱም ምናልባት እኛ በሌሎች ላይ ለመፍረድ እንቸኩላለን፥ እናም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዳለ እና መሐሪ መሆኑን እንረሳለን።

የእግዚአብሔርን ቃል በፍፁምነት የተከታተለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እመነታችን እና ፍቅራችን ፍጻሜ እንዲኖረው እርሷ በአማላጅነቷ ትርዳን።

 

12 February 2023, 10:48

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >